Saturday, March 25, 2017

አንድ እስረኛ ተመርምሮ ሲመለስ መጀመሪያ የሚቀርብለት ጥያቄ 'ተሰቅለህ ነበር ወይም አልተሰቀልክም? የሚል ነው"ከእስር የተለቀቁት አቶ ሐብታሙ አያሌው።




Habtamu Ayalew on VOA : says of something horrible at TPLF's torture centers which he is not willing to disclose on moral and religious grounds unEthiopian , . . You can easily guess that . . . A dehumanizing , demeaning Sexual abuse by security agents is widespread ,. . . Sad ! !
 In deed it's unEthipoian..... sodomy is the most inhuman barbaric act. 
But for me what I found even more shocking and hurt breaking is the fact that we the society seemed to no longer be outraged enough to rise up to say enough is enough and put a stop to it in order regain our dignity and humanity back....we keep saying 'oh that's sad' and that's it.
The former spokesman for the opposition party accused of terrorism offenses in prison are serious blow as a result of the investigation during the two years of suffering now say has included health crisis.

Brutalities perpetrated in prisons, degrading various types of diagnostic inidemiderigumi the same health problems, including his predecessor

Monday, October 24, 2016

የሕወሃት ወታደራዊ አገዛዝ !



የሕወሃት ወታደራዊ አገዛዝ የተጨማለቀ የሕግ ስርዓት :

የሕወሃት አገዛዝ አንዱ ባህሪዉና መለያው ዜጎችን ማሰቃየት ነው። ማሰር እንጂ መፍታት፣ መጣል እንጂ ማንሳት፣ መግደል እንጂ ማዳን፣ ማዋረድ እንጂ ማክበር፣ መስበር እንጂ መጠግን ፣ መከፋፈል እንጅ አንድ ማድርግ አያወቁበትም። እንደ እንስሳት ጉዳዮችና ልዩነቶችን በሃይልና በጡንቻ መፍታት እንጅ እንደ ሰለጠነ ሰው በሰለጠነ መንገድ መፍታት አለመፈለግ ብቻ ሳይሆን ብቃቱ የለዉም።

ለስሙ ፍርድ ቤት፣ ዳኛ፣ ሕግ ፣ ሕገ መንግስት እያሉ ህወሃቶች ጠዋትና ማታ ያሰለቹናል። ሆኖም ግን በኢትዮጵያ ታሪክ እንደነርሱ ሕግን መቀለጃና ማሾፊያ ያደረገ አገዛዝ የለም :የወያኔ የጅምላ እስራትና ግድያውን ቢያስፋፋም ሕዝባዊ ተቃውሞው እንደቀጠለ ነው

አሀኡነማ ሰው መግደለ ማሰረ መሰ ቃ የት ሕጋአው አደረጉተ ዱ ርአ ውነሰ ሀገአረዋት
ግን ግ ዜ ው ደረሰዋል: ወያኔ ዝቅ ብሎ የሚለምንበት !!

 

Tuesday, October 11, 2016

በህዝብ ላይ ጦርነት አውጆ ያሸነፈ የለም





የስርዓቱ መውደቅ ጫፍ ላይ ደርሷል። ከዚህ በኋላ የትኛውም ጥገና አያተርፈውም። በገንዘብ የሚፈወስ አይደለም። ደምወዝ በመጨመር የሚተርፍ አይደለም። ዘግይቷል። ረፍዷል። ህወሀት መጠየቅ ያለበት መውጪያ መንገድ ብቻ ነው።




የወያኔ የጊዜአዊ አዋጅ ድንፋታና የሆዳም የካዲሬዎቹ ጫጫታ ሕዝባዊ ትግሉን አይበገረውም። እንዲያውም አስቆጥቶና እልክ አሰግበቶ የበለጠ ሕዝቡን ወደ ትግል ያስገባዋል እንጂ ! ስለሆነም ይህንን ጉግ ማንጉግ፡ ሞራልና ሕሊና የሌለው፡ ከፀረ ሀይማኖትና ከፀረ እግዚአብሔር አልፎ ፡ ፀረ-የሰው ልጅ የሆነውን የመህይም ጥርቃሞ ቲፒ ኤል ኤፍ TPLF (ወያኔ/ኢሕአደግ) የሚባለውን የማፊያ ቡድን ከመላ ኢትዮጵያ ለማጥፋት... በዘር፡ በሀይማኖት፡ በፖሌቲካና በኢኮኖሚ ሳንለያይ አንድ ሁነን ታግለን የድሉን ቀን እናቅርበው እላለሁ። የወቀቱ መፈክር "እየተደራጁ መታገል፡ እየታገሉ ነፃነት" መሆን አለበት !

ከዚህ በኋላእኛ ስንሰርቅና ስንከብር እናንተ ዝም ብ ለችሁ ተመለከቱ በቃ ዘ ር ፍ በቃ !!! የትግራይ ነፃ አውጪው የወያኔ ከፍተኛ ባለስልጣናት 11% አገሪቱን አሳድገናል ብለው ነገር ግን ሃቁ ከ20 ሚሊዮን ህዝብ በላይ ከኃይለ ሥላሴም፣ ከደርግም እጂግ በከፋ ቁጥር ተርቦ እነሱን ለማትረፍ ዓለም በሚረባረብበት ጊዜ እነሱ ከኢትዮጵያ ህዝብ ሌት ከቀን በመዝረፍ አገር ውስጥ ከገነቡት ትላልቅ ህንፃ፣ ቪላና የተለያዩ ድርጅቶች ውጪ በተለያዩ ዓለማት የውጪ ባንኮች ያስቀመጡት ገንዘብ ብዛት በአሜሪካን ዶላር $ 22,572,000,000 (ሀያ ሁለት ቢሊዮን አምስት መቶ ሰባ ሁለት ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር

Thursday, August 25, 2016

የነጻነት ጮራ በኢትዮጵያችን በቅርቡ ይፈነጥቃል!!!!












የፈይሳ ሌሊሳ ቤተሰቦች ከሮይተርስ የዜና አውታር ጋር በመኖሪያ ቤቱ ቃለምልልስ አድርገዋል። ወላጅ እናቱ ''መንግስት ቢመለስ 

ምንም አይሆንም ብሏል። ምን ይመስልዎታል?''ተብለው ሲጠየቁ ይህን ምላሽ ሰጥተዋል።





''እኔ አላምንም እዛው ይሁንልኝ። ልጄን እወደዋለሁ ቢመጣልኝ እፈልግ ነበር ነገር ግን ምን አደርጋለሁ። ብዙ ቀናቶች ሳለቅስ አሳልፌያለሁ። አሁን ግን ጥሩ ስሜት ይሰማኛል። እዛው ባለበት እንዲሆንልኝ እፈልጋለሁ። እሱ ብቻ ባለበት ሰላም ይሁንልኝ እንጂ!''

ባለቤቱ በበኩሏ ''በወቅቱ በጣም ፍርሃትና ድንጋጤ ወሮኝ ነበር። ነገርግን አልተገረምኩም ምክንያቱም አውቀዋለሁና። በማኅበራዊ ድረገጾች ላይ የተገደሉ ሰዎችን አካል ሲያይ፣ ሲታሰሩና ሲደበደቡ ሲያይ ውስጡ ይቃጠል ነበር። ባደረገው ያልተገረምኩት የውስጡን ቁጭት ስለማውቀው ነው።''የነጻነት ቁንጮ የጀግኖቹ ጀግናምንም ሳይቸግራው ገንዘብ ወይ መኪና
ወርቅ ፣ናሃስ ፣ብር ሳይል ሳይበግረው ዝና :ሁለት ታዳጊ ሕጻናት ልጆቹን፣ አሮጊት እናቱን፣ ባለቤቱን ትቶ የወገኑን ብሶት በዓለም ዓደባባይ አሰምቷል። የነጻነት ጮራ በኢትዮጵያችን በቅርቡ ይፈነጥቃል። እስከዛው ፈይሳ ሌሊሳ ባለህበት ሰላምህ ይብዛ!!!
..
.



Tuesday, August 16, 2016

ኃላፊነት የማይሰማው መንግሥት ነው!!!



አንጋፋው የተቃውሞ ፖለቲከኛ ዶክተር መረራ ጉዲና ሀገራቸው ኢትዮጵያ አሁን ባለችበት ሁኔታ ወደ የእርስ በእርስ ጦርነት ውስጥ ለመግባት መንታ መንገድ ላይ መቆሟን ተናገሩ፡፡

"ብዙ ህዝብ ባለፉት 25 አመታት አገዛዙ በፈጸመበት ጭቆና መማረሩን የተናገሩት ዶክተር መረራ አሁን ላይ በየቦታው ሰዎች ለተቃውሞ በየአደባባዩ መውጣታቸውንና በዚህም የተነሳ ከፍተኛ የሰብአዊ ቀውስ እየደረሰ መሆኑን ጠቁመው ይህ ሁኔታ ባለበት ከቀጠለ ደግሞ የእርስ በእርስ ጦርነት ሊከሰት ይችላል የሚል ስጋታቸውን ገልጸዋል"

፡፡-+የተቃወመውን ወይም በቀጥታ ድጋፍ ያልሰጠውን ሁሉ ፀረ ሰላም፣ ፀረ ልማት፣ ፀረ ዴሞክራሲ፣ ደርግ ናፋቂ፣ የደርግ ርዝራዥ፣ የሻዓቢያ ተላላኪ፣ አሸባሪዎች፣ ኪራይ ሰብሳቢዎች ወዘተ የዕለት ከዕለት ማጣጣያ ከሆኑ ቆይቷል። ህገ መንግስቱ አክብረው፣ በሰላማዊ ትግል የሚታገሉ ድርጅቶችን የአሸባሪነት ስም በመለጠፍ ትግሉ አቅጣጫውን እንዲስት በመገፋፋት፤ ህብረተሰቡ ነፃ ሆኖ እንዳይኖር እንዳይናገር፣ እንዳይፅፍ፣ እንዳይቃወም፣ እንዳይደራጅ በስጋትና ጭንቀት በአገሩ ነፃ ዜጋ ሆኖ እንዳይኖር እየተደረገ ነው፡፡ ሀገሪቱ እኛ ከሌለን ያልቅላታል የሚሉ በስልጣን ላይ ያለው አካል ብቻ ነው ያለነሱ መሪ ያለነሱ አልሚ ያልነበረ ለወደፊቱም የማይኖር ማይመስላቸው ስልጣኑን አኝ አርገው አለቅ ያሉት ;;

ህዋሃትም በሰሞኑ ዘገባው ባለፉት ወራት ሲታዩ የነበሩትን ህዝባዊ ተቃውሞ እንደ ተራ ጩኸት እያጣጣለው ልክ እንደ ደርግ "በጩኸት የፈረሰች ከተማ እያሪኮ ብቻ ነች" የሚል አይነት እድምታ ያላቸው መግለጫዎች እያሰሙ ነው። ዛሬ እንዲህ አይነት መግለጫ ፍሬ ቢስ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ ቱኒዚያ፣ ግብፅ፣ ሊቢያ… በጩኸት ከፈረሱ በኋላ፡፡ በግብፅ አብዮት ወቅት አንድ የትጥቅ ትግል የሚያካሄድ ተቃዋሚ ድርጅትን ይመሩ የነበሩ ከማል ሀቢብ የተባሉ ሆስኒ ሙባረክ በወደቁ ማግስት Tahrir Square (በነፃነት አደባባይ) በአፕሪል18 ቀን 2011ዓ.ም ለታተመው Time መጽሔት "እኛ ለ40 አመት በጠመንጃ መገልበጥ ያልቻልነውን ህዝቡ ያለአንዳች የጦር መሳሪያ በ18 ቀን ውስጥ እውን አደረገው" ብለው በመገረም ተናግረዋል።

ሰላማዊ ህዝባዊ የአደባባይ ተቃውሞና ጩኸት መንግስትን ባያሰጋው ኖሮ ለምን ሰው አደባባይ እንዳይወጣ ይከለክላል?

እሪሪሪ ብሎ መጮህ ነፃነት ያስገኛል። ስለዚህ እንጩህ !!

Friday, February 19, 2016

አገሪቷ ትልቅ ችግር ላይ ናት !





ኦሮሚያ ክልል የጦርነት ቀጠና ሆናለች። እነ ጀነራል ሶሞራ በጭካኔና በግፍ ሕዝቡን በጥይት እያረገፊት ነው"" ባለፉት 3፣ 4 ቀናት ብቻ ቢያንስ ወደ መቶ የሚጠጉ ወገኖቻችን ተገድለዋል። "ቢያንስ" የሚለው ላይ አስመርበታለሁ። ለምን እጅግ በጣም ብዙ የቆሰሉ አሉ። የቆሰለ ሁሉም ይደናል ማለት አይደለም። ሃኩም ሄዶ መሞትም አለ።፡

በጣም ያሳዝናል.....በጣም ልብን ያደማል። አለም በሰለጠነችበት በዚህ 21ኛው አለም፣ እንደ ረሃብ፣ ድርቅ፣ ድህነት የመሳሰሉ የሁላችንም ትኩረት የሚያስፈልጋቸው ችግሮች እያሉን፣ በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንደሚባለው፣ በአጋዚዎች እጆች ላለፉት 25 አመታት እንደነበረው አሁን ዜጎች እየተገደሉ መሆናቸው በጣም ይሳዝናል።

በሜዳ ላይ ያለውን ሁኔታ እንደሚያሳየው ተቃዉሞው በጣም ተባብሷል። ከአዲስ አበባ ወደ ሃረር ፣ ከአዲስ አበባ ወደ ነቀምቴ ፣ ከነቀምቴ ወደ ጂማ፣ ከሻሸመኔ ወደ ባሌ ....የሚወስዱ መንገዶች ተዘግተዋል። በብዙ ቦታዎች የኦሮሚያ ክልል የጸጥታ ኃይሎች በቀጥታ ከፌዴራሎች ጋርም ግብግብ የፈጠሩበት ሁኔታ ነው ያለው። ሰላማዊ የሆነው እንቅስቃሴ፣ ወያኔዎች የኃይል እርምጃ በወሰዱ ቁጥር ወደ አመጽ መሸጋገሩ አይቀርም። እየተሸጋገረም ነው።


አገሪቷ ትልቅ ችግር ላይ ናት !

‎OromoProtest‬

Saturday, December 19, 2015

የመንግሥት ኃይሎች ኦሮሚያ ውስጥ እየወሰዱ ያሉት እርምጃ “እጅግ አስከፊ” ወይም በእንግሊዝኛው ቀጥተኛ አባባል “ብሩታል

"ጥቂቶች በብርሀን ፍጥነት ተዝቆ ወደማያልቅ ሀብት የተመነጠቁበት መንኮራኩር፣ መሬት "

ከ5 ዓመታት በፊት እኚህ ክቡር ሰው ሲናገሩ መስሚያ ጆሮ ቢኖራችሁ ዛሬ መያዣ መጨበጫ ባልጠፋችሁ። በነገራችን ላይ ይህ የአቶ በቀለ ገርባ ንግግር እና የአቶ አንዷለም አራጌ ንግግር ምንጊዜም ልቤን የሚያነሳሳኝ፣ በሀገሬ ተስፋ ከሚሰጡኝ መሳጭ ንግግሮች ዋነኞቹ ናቸው

ሀገር መምራት ቀላል እንዳልሆነ እናውቃለን ነገር ግን ከዓመት ዓመት የሕዝቡን ብሶት እያዳመጠ እየተሻለው፣ ልምድ እየቀሰመ ሀገሪቱን ሕዝቡን ወደፊት ማራመድ ሲገባው ከዕለት ወደ ዕለት ወደኋላ እየተመለሰ፣ የኋሊት እየሄደ ሀገሪቱን መምራት ወደማይችልበት ደረጃ ደርሷል::

የኤፌድሪ ሕግ መንግስት እንደሚናገረው ፣ የገዢው ሥርዓት የፖሊሲ ሰነድ እንደሚገልጸው መሬት የመንግስት እና የሕዝብ ነው ይላል:: ነገርግን መሬት የሕዝብ ነው፣ የመንግስት ነው፣ የሁለቱም ነው? መሬት የማንም አይደለም:: መሬት የገዢ ባለስልጣኖች የግል ንብረት ነው::

እንደፈለገ የሚሸጡት፣ የሚለውጡት፣ ጓደኛ የሚያፈሩበት፣ በዘመድ አዝማድ የሚያከፋፍሉት፣ ለወገን እያሉ ለነሱ ፓርቲ አባላት መመልመያ የሚጠቀሙበት ማማለያ ነው መሬት::

*መሬት የተማረውን ሳይቀር፡ ምሁሩን ሳይቀር ማሳወርያ ሆኗል። ዛሬ ምሁሩን አንዳንድ ቦታ በአበዛኛው በምንመለከትበት ጊዜ ስለፍትሕ፣ ስለመብት፣ ስለ እኩልነት የማያወራበት ጊዜ ደርሷል።ምክንያቱ ይኼ ማሳወርያ ነው ዛሬ በየከተማው እና በአዲስ አበባ ዙርያና ሌሎች ከተሞች አካባቢ በብዛት መሬት እየተሰጣችው አፋቸው ተሸብቧል።ስለዚህ መሬት አፍ መሸበቢያ ነው።

* መሬት ለፖለቲካ ፍጆታ ሲባል ውጭ የሚኖረውን ኢትዮጵያዊ መሳቢያ ማግኔት ሆኗል። ዳያስፖራ እየተባለ በአንድ ወቅት ግር... ብለው መጥተው፣ እዚህ ወገኖቻችን ሜዳ ላይ ወድቀው አንዲት ስንዝር መሬት የሌላቸው ወገኖች እያሉ በውጭ ቢያንስ ቤት ውስጥ የሚኖሩ ሰዎች መጥተው መሬት ተቀራምተው ሽጠውት ሄደዋል። ስለዚህ ማግኔት ነው የምንለው ለዚህ ነው።
*መሬት ዛሬ ጥቂቶች በብርሀን ፍጥነት ተዝቆ ወደማያልቅ ሀብት የተመነጠቁበት መንኮራኩር ነው።
ብንመለከት፣ እነድውም አንዳንዶቹን ሀብታሞች ብንጠይቃቸው... በሕዝቡ ዘንድ "ታሪኬ በአጭሩ" እየተባሉ የሚጠሩ አሉ። "እንዴት ነው፣ ይህ ሀብት ከየት መጣ እንዴት አገኛችሁ?" ተብለው ቢጠየቁ "እንደዚህ አድርጌ፣ እንደዚህ ለፍቼ አመጣሁ..." ማለት እንኳ የማይችሉ፣ገንዘቡን እንዴት እንዳፈሩት የማያውቁ...ስለዚህ ዛሬ መሬት እንደዚህ ነው:: መሬት የምንም አይደለም
መሬት ወሳኝ ሀብት መሆኑን እናውቃለን::
እኛ ኢትዮጵያዊያን ከዚህ ሀብት ጋራ ባለን ግንኙነት ምክንያት የዜገነት ደረጃችን በ4 ቦታ የተከፈለ ይመስለኛል:-->

1.መሬቱን የሚሸጡ አሉ አንደኛ ደረጃ ዜጎች
2.መሬቱን ከነሱ የሚቀበሉ አሉ፣ ሁለተኛ ደረጃ ዜጎች

3.እነሱ ሲቀባበሉ ቁጭ ብሎ ትዕይንቱን የሚመለከተ ዜጋ ደግሞ አለ ፤ ሦስተኛ ደረጃ- የበይ ተመልካች
4.መሬቱን ተነጥቆ፣ እትብቱ ከተቀበረበት፣ ተወልዶ ካደገበት መሬቱ ሥፍራ እየተባረረ መሬቱ ለሌላ የሚሰጥ የዚህ ድርጊት ሰለባ የሆነ አርሶ አደር ደግሞ አለ::

እኛ ምንታገለው ለዚህ ነው!!!

*****ደግማችሁ ደጋግማችሁ አድምጡት፣ የተቃውሞው መሠረታዊ ጥያቄዎች ያልገባችሁ ፍንትው ይልላችኋል። ይህ የጭቁን ኢትዮጵያዊያን ጥያቄ ነው!
የመንግሥት ኃይሎች ኦሮሚያ ውስጥ እየወሰዱ ያሉት እርምጃ “እጅግ አስከፊ” ወይም በእንግሊዝኛው ቀጥተኛ አባባል “ብሩታል” ናቸው ሲል ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ቡድን አምነስቲ ኢንተርናሽናል አውግዟል