Sunday, December 30, 2012

ፓርላማው የአቶ ጁነዲን ሳዶን ያለመከሰስ መብት ሊያነሳ ነው


ፓርላማው የአቶ ጁነዲን ሳዶን ያለመከሰስ መብት ሊያነሳ ነው

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት (ፓርላማ) በቅርቡ ከሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትርነታቸው የተነሱትን የአቶ ጁነዲን ሳዶ ያለመከሰስ መብት ሊያነሳ መሆኑን ቅርበት ያላቸው ምንጮች ገለጹ፡፡
የምክር ቤቱ አባል የሆኑ ምንጮች  እንደገለጹት፣ አቶ ጁነዲን በፓርላማ የሥነ ሥርዓት ደንብ መሠረት ሊጠየቁበት የሚችል የሕግ ጉዳይ ሊኖር ስለሚችል፣ በምክር ቤት አባልነታቸው ያገኙትን ያለመከሰስ መብት ምክር ቤቱ እንዲያነሳ የሚጠይቅ ደብዳቤ በመንግሥት ቀርቧል፡፡ ጥያቄው በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ኩማ ደመቅሳ ወይም በፍትሕ ሚኒስትሩ አቶ ብርሃን ኃይሉ በኩል መቅረብ ያለበት መሆኑን የምክር ቤቱ ደንብ ያዛል የሚሉት እነዚሁ ምንጮች፣ ጥያቄው በየትኛው አካል መቅረቡን ለመረዳት እንዳልቻሉ አስረድተዋል፡፡
የአንድ የምክር ቤት አባልን የሕግ ከለላ ስለማንሳት የቀረበ የውሳኔ ሐሳብን መርምሮ ማፅደቅ” የሚል ቢሆንም፣ የምክር ቤቱ አፈ ጉባዔ አቶ አባዱላ ገመዳ ይህንን አጀንዳ በቀጣይ ስብሰባ ለመመልከት ላልተወሰነ ጊዜ አስተላልፈውታል፡፡

የምክር ቤቱ አባላት ለጉባዔው የሚቀርቡ አጀንዳዎችን ቀደም ብለው በማወቅ በጉዳዩ ላይ የሚቀርቡ ሰነዶች ካሉ ደግሞ ሰነዶቹ ከውይይቱ ሦስት ቀናት በፊት እንዲደርሳቸው የምክር ቤቱ የአሠራር ደንብ ቢደነግግም፣ የሕግ ከለላን ስለማንሳት ቀርቦ ስለነበረው አጀንዳ የቀረበላቸው ምንም ዓይነት ሰነድ እንደሌለ ምንጮች ተናግረዋል፡፡ 
የሕግ ከለላው እንዲነሳ ጥያቄ የቀረበበት የምክር ቤት አባል ማንነት በይፋ ባይገለጽም፣ ይፋዊ ባልሆነ መንገድ የአቶ ጁነዲን ሳዶ ጉዳይ መሆኑን እንደተረዱ ተናግረዋል፡፡
አቶ ጁነዲን ሳዶ በአሁኑ ወቅት በሽብር ተግባር ተጠርጥረው በእስር ላይ ከሚገኙት ባለቤታቸው ወ/ሮ ሐቢባ መሐመድ ጋር በተያያዘ፣ በድርጅታቸው ኦሕዴድ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ተገምግመው ከፓርቲው ከፍተኛ አመራርነት ወደ ተራ አባልነት ዝቅ መደረጋቸው ይታወሳል  አቶ ጁነዲን ሳዶ በአሁኑ ወቅት በሽብር ተግባር ተጠርጥረው  ከሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትርነታቸው መነሳታቸውን ተዘግቧል፡

Sunday, December 23, 2012

ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋና እነ አንዱዓለም አራጌ የይግባኝ ክርክራቸውን አጠናቀቁ!!!


ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋና እነ አንዱዓለም አራጌ የይግባኝ ክርክራቸውን አጠናቀቁ!!!

        



--------ኢሳትም የመገናኛ ብዙኃን እንጂ የአሸባሪ ድርጅት ሚዲያ አለመሆኑን ማረጋገጣቸውን <  አቶ ደርበው ገልጸዋል፡፡ 
--------ለአንድ ዓመት ከሦስት ወር መሬት ላይ እንዲተኛ መደረጉን
---------ትንሽ ብርሃን ባለበት በጨለማ ክፍል ውስጥ ከስድስት ሰዎች ጋር መታሰሩን
-------- የመተንፈስ ችግር እንዳለበት
---------ከተወሰኑ ቤተሰቦቹ በስተቀር ሌላ ሰው እንዳይጠይቀው መከልከሉን አስረድቷል
                                                                                                                            አንዱዓለም አራጌ
በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሦስተኛ ወንጀል ችሎት በሽብርተኝነት ወንጀል ክስ ተመሥርቶባቸው በ18፣ በ25 ዓመታትና በዕድሜ ልክ እስራት ተቀጥተው በእስር ላይ የሚገኙት ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ናትናኤል መኮንን፣ ክንፈሚካኤል አበበ (አበበ ቀስቶ) እና አንዱዓለም አራጌ ቅጣታቸውን በመቃወም ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ባቀረቡት የይግባኝ አቤቱታ ላይ ከዓቃቤ ሕግ ጋር ታህሳስ 10 ቀን 2005 ዓ.ም. ክርክር አድርገው አጠናቀቁ፡፡ አንዱዓለም አራጌ፣ ናትናኤል መኮንንና ክንፈሚካኤል አበበ (አበበ ቀስቶ) ክርክራቸውን ያደረጉት በጠበቃ ተወክለው ሲሆን፣ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ግን ክርክሩን ያደረገው ያለጠበቃ በራሱ ነው፡፡ 

ጋዜጠኛ እስክንድር ለፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ያቀረበው ወይም ባደረገው ክርክር ላይ በዋናነት ያነሳው ነጥብ፣ የግንቦት 7 ድርጅት አባል ስለመሆኑ የተገኘበት መረጃም ይሁን የሰው ምስክር በዓቃቤ ሕግ እንዳልቀረበበትና “አባል ነው” መባሉም ፍፁም ሐሰት መሆኑን ነው፡፡ በሥር ፍርድ ቤትም በዋናነት ሲከራከርበት የነበረበትንና “የግንቦት 7 ዓባል ስለመሆኔ ዓቃቤ ሕግ ምንም ዓይነት ማስረጃ ባላቀረበብኝና ባልተመሰከረብኝ ሁኔታ እንዴት ልቀጣ እችላለሁ?” የሚለውን ሐሳብ ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ባቀረበው የክርክር ሐሳብም በዋናነት ተናግሯል፡፡ 

ዓቃቤ ሕግ በሥር ፍርድ ቤት ላቀረበበት ክስ በዋና ማስረጃነት ያቀረበው  በተለያዩ የመገናኛ ብዙኃን የተናገራቸውንና የጻፋቸውን የተለያዩ መጣጥፎች፣ እሱን ጨምሮ ሰባት ሆነው ሊመሠርቱት ስለነበረ የሲቪክ ማኅበር መመሥረቻ ጽሑፍ እንጂ የሰው፣ የሰነድም ሆነ የኢ-ሜይል ማስረጃዎች እንዳልቀረቡበትና በፍፁም የግንቦት 7 ድርጅት አባል አለመሆኑን አስረድቷል፡፡  

ዓቃቤ ሕግ እንደ ዋና ማስረጃ ያቀረበበት በመስከረም ወር 2004 ዓ.ም. ሰላማዊ ሠልፍ ለማድረግ ሲንቀሳቀሱ ከነበሩት የመኢዴፓ ዋና ጸሐፊ ከአቶ ዘመኑ ሞላ ጋር ያደረገውን ንግግር መሆኑን ጋዜጠኛ እስክንድር አስረድቷል፡፡ አቶ ዘመኑ ወደሱ መጥቶ ሰለ ሰላማዊ ሠልፉ ምክር ሲጠይቀው፣ ሰላማዊ ሠልፍ ለማድረግ ወቅቱ እንዳልሆነ፣ ሠልፍ የሚያደርጉም ከሆነ በማንኛውም መንገድ የውጭ ኃይሎች እጅ ሊኖርበት እንደማይገባኧ የገንዘብ እጥረት ቢኖርባቸው እንኳን እሱም ቢሆን በገንዘብ ሊረዳቸው እንደሚችል ከመመካከር ውጭ፣ አንዲትም ቃል ስለአመፅና ረብሻ ተነጋግረው እንደማያውቁ ለፍርድ ቤቱ አስረድቷል፡፡ አቶ ዘመኑም በሥር ፍርድ ቤት ለዓቃቤ ሕግ ምስክር ሆነው በቀረቡበት ወቅት ያረጋገጡት ይህንኑ መሆኑንና ፍርድ ቤቱ የሥር ፍርድ ቤት መዝገብን ሊመለከተው እንደሚገባ ጠቁሟል፡፡ 
ዓቃቤ ሕግ በሰሜን አፍሪካና በዓረብ አገሮች የተቀሰቀሰውን አመፅ ወደ ኢትዮጵያ ለማምጣት የተለያዩ እንቅስቃሴዎችን ሲያደርግ ነበር በማለት ስላቀረበበት ክስ ጋዜጠኛ እክስንድር ለፍርድ ቤቱ ሲያስረዳ፣ “ዓቃቤ ሕግ ይህንን ሐሳብ ወይም ክስ ያቀረበው እኔ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ያቀረብኳቸውን መጣጥፎች በግንቦት 7 ልሳን ላይ ስላገኛቸው እንጂ፣ ምንም ዓይነት እውነተኛ ማስረጃ አግኝቶ አይደለም፡፡ ይህ ደግሞ እንኳን ለተቃውሞ የቆመ ድርጅትን ቀርቶ ማንም ከተለያዩ ድረ ገጽ ላይ ወስዶ ራሱ በፈለገው ቅርፅና አመለካከት ቀይሮ ሊያቀርበው ይችላል፡፡ የእኔን ብቻ ሳይሆን ማንኛውንም መጣጥፍ እንደፈለጋቸው የሚያደርጉ ናቸው፤” ብሏል፡፡ 

የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉ በተሳሳተ ሁኔታ እየተተረጐመ መሆኑን የጠቆመው ጋዜጠኛ እስክንድር፣ ሌላው የተከሰሰበት ወንጀል የፀረ ሽብርተኝነት ሕጉን አንቀጽ 23 ተላልፏል በሚል መሆኑን ተናግሯል፡፡ ዓላማውም እንደ ዓረብ አገሮች የመንግሥትን ሥልጣን በኃይል ለመያዝ መሆኑን ዓቃቤ ሕግ በክሱ ማስረዳቱን የገለጸው ጋዜጠኛው፣ በዓረብ አገሮች ማለትም በግብፅ፣ በቱኒዝያ፣ በሊቢያ፣ በየመንና በሶሪያ የተደረገው አመፅ ዓቃቤ ሕግ ከሚለው በእጅጉ የተለየ መሆኑን አስረድቷል፡፡ “የሥር ፍርድ ቤት በኃይል ሥልጣን ለመያዝ የዓረብ አገሮች የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ ዓላማ መከተልህ ትክክል አይደለም” በማለት ፈርዶብኛል፡፡ እኔ በፖለቲካ ድርጅት ተመርቼ ያደረግኩት እንቅስቃሴ የለም፡፡ ለአገሬ ይጠቅማል ብዬ ስላመንኩና አሁንም ስለማምን፣ ሕገ መንግሥቱን የተከተለ ዓላማ ነው ያለኝ፡፡ በዓረብ አገሮች የተደረጉ አመፆች በፖለቲካ ድርጅት የታገዙ አይደሉም፡፡ የታገሉት ወይም እየታገሉት ያለው ለነፃነትና ለፍትሕ ነው፡፡ ይህንንም ድርጊታቸውን የአፍሪካ ኅብረት ሙሉ ዕውቅና ሰጥቶታል፡፡ ይህ ድርጊታቸው እንደ ምሳሌ እንጂ እንደ ተቃውሞ ሊወሰድ አይገባም፡፡ አድርገሃል ስለተባልኩት ነገር ሁሉ አንድ ማስረጃ ከተገኘ ጥያቄዬን አነሳለሁ፤” ብሏል፡፡ በግልጽ ያደረጋቸው ቃለ ምልልሶች፣ በአንድነት ፓርቲ ላይ ንግግር እንዲያደርግ ተጋብዞ ያደረጋቸው ንግግሮችና በተለያዩ ጋዜጦችና ድረ ገጾች ላይ በግልጽ የጻፋቸውን መጣጥፎች፣ ዓቃቤ ሕግ በማስረጃነት ከማቅረቡ ውጭ ምንም ዓይነት የተደበቀና ሚስጥር ነው የተባለ ማስረጃ እንዳላቀረበበት ጋዜጠኛ እስክንድር አስረድቷል፡፡ 


Thursday, December 20, 2012

አራት ኢትዮጵያዊን ጋዜጠኞች የሄልማን/ሃሜት ተሸላሚ ሆኑ





አራት ኢትዮጵያዊን ጋዜጠኞች የሄልማን/ሃሜት ተሸላሚ ሆኑ

መስፍን ነጋሽ ,ውብሸት ታየ ,እስክንድር ነጋ ,ርዕዮት ዓለሙ
አራት ኢትዮጵያዊያን ጋዜጠኞች የሚዲያ ሥራ በዓለም እጅግ አዳጋች በሆነበት ሀገራቸው ሃሣብን በነፃ የመግለፅ መብቶች እንዲከበሩ ላደረጓቸው ጥረቶች (እአአ) የ2012ን ስመ-ጥሩን የሄልማን/ሃሜትን ዓለምአቀፍ ሽልማት አግኝተዋል


በሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቹ ድርጅት በሂዩማን ራይትስ ዋች አስተዳደር ጥላ ሥር የሚገኘው ሄልማን/ሃሜት በዓለም ዙሪያ ለሚገኙ የፖለቲካና ሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ዒላማ ለሆኑ ደራሲዎችና ጋዜጠኞች ሽልማቱን የሚሰጠው በያመቱ ነው።

ስመ ጥሩ ሽልማት መጠሪያውን ያገኘው እአአ በ1950ዎቹ ፀረ-ኮሚኒስት ምርመራዎች ወቅት ወከባ ከደረሰባቸው ሁለት ጋዜጠኞች ከሊልያን ሄልማን እና ዳሸል ሃሜት ነው።

እስክንድር ነጋ ፈንታ፥ ነፃ ጋዜጠኛና ብሎገር ወይም የኢንተርኔት አምደኛ፥
​​

ርዕዮት ዓለሙ ጌቤቦ፥ በታገደው ሣምንታዊ “ፍትሕ” ጋዜጣ አምደኛ፥
​​
ውብሸት ታየ

ውብሸት ታየ አበበ፥ የተከለከለው ሣምንታዊ “አውራምባ ታይምስ” ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ፥
​​
መስፍን ነጋሽ

የ “አዲስ ነገር Online” አዘጋጅ መስፍን ነጋሽ፥ የዘንድሮውን ሽልማት ካገኙ  ከ 19 ሀገሮች የተውጣጡ 41 ጋዜጠኞችና ፀሀፊዎች መካከል ናቸው።
​​
እስክንድር፥ ርዕዮትና ውብሸት ባሁኑ ወቅ ኢትዮጵያ ውስጥ በእሥር ላይ የሚገኙ ሲሆን፥ የአዲስ ነገሩ መስፍን ነጋሽ ግን፥ እአአ በ2009 ዓ.ም ሀገሩን ጥሎ ወጥቶ በስደት ላይ ይገኛል።

ባጠቃላይ አራቱም ግን በሀገሪቱ በፀረ ሽብር ሕግ መሠረት በዚህ ዓመት ጥፋተኞች ተብለው ተፈርዶባቸዋል።

Tuesday, December 18, 2012

እስክንድር ነጋ እንዲፈታ የአውሮፓ ፓርላማ አባላት ጠየቁ


እስክንድር ነጋ እንዲፈታ የአውሮፓ ፓርላማ አባላት ጠየቁ





የአውሮፓ ፓርላማ 16 አባላት በጋዜጠኛና የኢንተርኔት አምደኛው እስክንድር ነጋ የተራዘመ እሥር የተሰማቸውን ብርቱ ሥጋት በመግለፅ ለጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሣለኝ ደብዳቤ ፅፈዋል፡

የደብዳቤውን ይዘት እና የተፃፈበትን ምክንያት አስመልክቶ የቪኦኤ የአፍሪካ ቀንድ አገልግሎት ኃላፊ ፒተር ሃይንላይን “ፍሪደም ናው” የሚባለውን ተቀማጭነቱ ዋሽንግተን ዲሲ የሆነ በነፃነትና በፖለቲካ እሥረኞች ጉዳዮች ላይ የሚሠራ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት የፕሮግራም ጠበቃ ፓትሪክ ግሪፊትዝን አነጋግሯል፡፡
እስክንድር ነጋ
​​
“የአቶ እስክንድር መታሠር በዓለምአቀፍ ደረጃ ጥበቃ የሚደረግለትን ሃሣቡን በነፃነት የመግለፅ መብቱን የተጋፋ ነው፡፡ ደብዳቤውን የፃፉት የአውሮፓ ፓርላማ አባላት ጠቅላይ ሚኒስትሩን የጠየቁት እስክንድር ነጋ ሳይዘገይ እና ያለአንዳች ቅድመ ሁኔታ እንዲፈታ ሥልጣናቸው የሚፈቅድላቸውን ሁሉ እንዲያደርጉ ነው፡፡“ ብለዋል ፓትሪክ ግሪፊትዝ፡፡

“ግልፅነት ይጎድለዋል” እየተባለ በሚተቸው ፀረ-ሽብር ሕግ የተከሰሰው ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ የ18 ዓመት እሥራት ተፈርዶበት ወህኒ እንደሚገኝ ይታወቃል፡፡

ከዓመት በፊት ታስሮ ለሁለት ወራት ያህል ከጠበቆች ጋር እንዳይገናኝ ተደርጎ መቆየቱን የሚያስታውሰው ዛሬ የወጣው የ“ፍሪደም ናው” መግለጫ እስክንድር የታሠረውና ተከስሦም የተፈረደበት የዐረቡን ዓለም አብዮት ዓይነት ንቅናቄ ኢትዮጵያ ውስጥም ሊከሰት እንደሚችል የሚናገር ፅሁፍ በኢንተርኔት በማውጣቱና በግልፅም በመናገሩ እንደነበረ ጠቁሟል፡፡
ደብዳቤው የኢትዮጵያ መንግሥት ሃሣብን በነፃነት የመግለፅ መብትን የማክበር ግዴታ እንዳለበት ያስታውስና አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር ኢትዮጵያን በሰብዓዊ መብቶች ጉዳዮች ላይ ወደፊት እንዲመሩና ከመንግሥታት ማኅበረሰብ ቤተሰብነት ያቀላቅሏት ዘንድ የተለየ ዕድልና አጋጣሚ ያላቸው መሆኑን ያሣስባል፡፡
Voa Amharic

Monday, December 17, 2012

ETHIOPIAN MUSLIM ACTIVISTS DENY TERROR CHARGES

ETHIOPIAN MUSLIM ACTIVISTS DENY TERROR CHARGES
BY KIRUBEL TADESSE 
Ap


ADDIS ABABA, Ethiopia (AP) -- A group of more than two dozen Ethiopian Muslims pleaded not guilty on Monday to charges of terrorism.
Federal prosecutors are accusing the group, which includes prominent clerics and journalists, with terrorism and attempts to create an Islamic state that would undermine the country's secular constitution. Among the 28 pleading not guilty was the wife of a former senior Cabinet minister who was fired last month after publicly defending her. One defendant did not plead and instead said he was mentally unfit to stand trial.
"I have not committed any crimes but a crime has been committed against me," one defendant told the court.
The charges come amid running confrontations between authorities and Muslim protesters who accuse the government of unconstitutionally encouraging a moderate teaching of Islam called Al-Ahbash. Some of protests turned violent and eight people were killed in two spate incidents in regional towns.
The group of 29, through their 11 lawyers, had challenged the charges as unconstitutional. A three-judge panel at the country's federal court disagreed in a ruling read out Monday.
For over a year protesters at a mosque in the capital, Addis Ababa, have demanded that the government stop meddling in their religious affairs.
Right groups blame the government for the latest tension with the Muslim community. Amnesty International says the protests were first triggered when the state started "unconstitutionally meddling" in religious affairs and squashed peaceful protests with "excessive force." The United States Commission on International Religious Freedom has said the charges are part of an attempt to "crush" members of the opposition.
The Ethiopian government blames "extremists" for the ongoing protests.
"Despite the allegation of the USCIRF, it has consistently been the position of the government, both in theory and in practice, that religion is constitutionally excluded from the dominion of the state," the country's Ministry of Foreign Affairs said in a statement.
The judges said the case would reconvene Jan. 22 to hear from the witnesses of the prosecution

Thursday, December 13, 2012

አቶ በቀለ ገርባና ሌሎች ስምንት ተከሳሾች ከሦስት ዓመታት እስከ 13 ዓመታት በሚደርስ ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ትናንትና ተወሰነባቸው

<<በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የውጭ ቋንቋ መምህርና የመድረክ ፓርቲ አመራር አቶ በቀለ ገርባና ሌሎች ስምንት ተከሳሾች ከሦስት ዓመታት እስከ 13 ዓመታት በሚደርስ ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ትናንትና ተወሰነባቸው
አንደኛ ተከሳሽ የነበሩት አቶ በቀለ ገርባን በስምንት ዓመታት፣ የኦህኮ ፓርቲ አመራር የነበሩትን አቶ ኦልባና ሌሊሳን በ13 ዓመታት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ትዕዛዝ አስተላልፏል፡፡ 

ሌሎቹ ተከሳሾች ማለትም ወልቤካ ለሜ፣ መሐመድ ቡሳ፣ ሐዋ ዋቆ፣ ደረጀ ከተማ፣ አዲሱ ሙከሪና ገልገሎ ቱፋ ከሦስት እስከ 12 ዓመታት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ወስኗል፡፡ አቶ በቀለ ገርባ፣ አቶ ኦልባና ሌሊሳና አቶ ገልገሎ ቱፋ ለአራት ዓመታት ከማንኛውም ማኅበራዊ መብቶቻቸው ታግደዋል፡፡ ሌሎቹም ለሁለት ዓመታት ታግደዋል፡፡ 
ተከሳሾቹ የቅጣት ማቅለያ እንዲያቀርቡ ሲጠየቁ አቶ በቀለ ጥፋተኛ አለመሆናቸውንና አድርገዋል በተባሉት ጉዳይ ላይ ምንም ነገር እንዳልፈጸሙ፣ ለኦሮሞ ሕዝብ ነፃነት ሲታገሉ ሕዝቡን በድለው ከሆነ ይቅርታ እንዲያደርግላቸው ከመጠየቅና ባለቤታቸው በእሳቸው ምክንያት ከሥራ በመባረራቸው ልጆቻቸው ያለ ገቢ ከመኖራቸው በስተቀር፣ ምንም ያጠፉት ነገር እንደሌለ ገልጸዋል፡፡ አቶ ኦልባናም ለምን እንደታሰሩ አለማወቃቸውን ከመግለጽ በስተቀር ምንም ባለማለታቸው በሁለቱም ላይ ቅጣቱ ከብዶ ተወስኗል፡፡ 

ኢትዮጵያ በ2012 ጋዜጠኞችን በማሰር ከአፍሪካ ከፍተኛውን ቁጥር ይይዛላ ች !



ኢትዮጵያ በ2012 ጋዜጠኞችን በማሰር ከአፍሪካ ከፍተኛውን ቁጥር ይይዛላ ች !

ክሱ ተቋርጦ በነፃ የተሰናበተው የፍትሕ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ 

ክስ እንደገና ተጀመረ!


ከነሐሴ 23 ቀን 2003 ዓ.ም. ጀምሮ በተለያዩ ጊዜያት በፍትሕ ጋዜጣ ላይ በራሱና በጽሑፍ አቅራቢዎች አምስት ጊዜያት ታትመው በወጡ መጣጥፎች ምክንያት ክስ ተመሥርቶበት፣ ነሐሴ 17 ቀን 2004 ዓ.ም. የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 16ኛ ወንጀል ችሎት ቀርቦ ዋስትና በመከልከሉ ማረሚያ ቤት እንዲቆይ መደረጉ ይታወሳል፡፡ 
ዓቃቤ ሕግ ላለፉት ሦስት ወራት አቋርጦት በድጋሚ በተንቀሳቀሰው ክስ ውስጥ ጋዜጠኛ ተመስገን በተለያዩ ጊዜያት ዕትሞች ‹‹ሞት የማይፈሩ ወጣቶች፣ የብሔር ብሔረሰቦች ቀን እስከ መጨፈር፣ የሁለተኛ ዜግነት ሕይወት እስከመቼና ሲኖዶስና መጅሊስ የአብዮታዊ ዲሞክራሲ ማጥመቂያ›› የሚሉ መጣጥፎች ማወጣቱ ተገልጿል

<<<<ፍርድ ቤቱ በሁለተኛነት ክስ የተመሠረተበትና የፍትሕ አሳታሚ የሆነው ማስተዋል የሕትመትና የማስታወቂያ ድርጅትም እንዲቀርብ አዞ፣ ክሱ መቀጠል አለመቀጠሉን በሚመለከት ብይን ለመስጠት ለታህሳስ 24 ቀን 2005 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡
ፍትሕ ጋዜጣ ሐምሌ 13 ቀን 2004 ዓ.ም. ለሕትመት ወደ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ድርጅት የገባ ቢሆንም፣ ‹‹ፍትሕ ሚኒስቴር እንዳታትም ብሎኛል›› በሚል ምክንያት ማተሚያ ቤቱ አላትምም ማለቱ ይታወሳል::
ጋዜጣው በወቅቱ ለምን እንዳልታተመ እስካሁን በግልጽ የተገለጸ ነገር ባይኖርም፣ በወቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር በነበሩት  መለስ ዜናዊ ሕመምና በአጠቃላይ በወቅቱ ስለነበሩበት ሁኔታዎች የሚያትት መጣጥፍ ይዞ ስለነበር፣ ጋዜጣው ከዚያን ጊዜ አንስቶ ተዘግቶ የቆየ ቢሆንም፣ ጋዜጠኛ ተመስገን በማኔጂንግ ኤዲተርነት ‹‹አዲስ ታይምስ›› በሚባል መጽሔት ላይ እየሠራ ይገኛል

Monday, December 10, 2012

የታህሳስ ግርግር ሊደገም ይሆን?

የታህሳስ ግርግር ሊደገም ይሆን?     

                                                             
By Temesgen Desalegn

መነሻ ታሪክ
ለዘመናት በኢትዮጵያውያን ጫንቃ ላይ በመጣበቅ ‹‹ቫምፓየር›› ሆኖ የነበረው የአጼ ኃይለስላሴ አገዛዝ አጥንት ድረስ ዘልቆ የሚሰማ ቁጭትና ኃዘኔታ የፈጠረባቸው ጥቂት ሰዎች ነበሩ፡፡ ግርማሜ ነዋይና አባሪዎቹ፡፡ 
ከሀገሪቱ ህዝብ ከ85 በመቶ በላይ የሚሆነው ‹‹አፈር ገፍቶ›› አዳሪ ቢሆንም፣ ጉልተኛው ስርዓት የወዙን ሲሶ ብቻ እንዲያገኝ ነበርና የተፈቀደለት፣ ከዓመት ዓመት በረሃብ እንዳለቀ፣ ጎጆው ከኃዘን ጋር ጋብቻ እንደፈፀመ፣ ህፃናት ልጆቹ ጠግበው ሳይበሉ፣

 እንደ ልጅ ሳይቦርቁ በልጅነታቸው ዳግም ወደ ማይመለሱበት ዓለም መሄዳቸው ከማንም በላይ ያንገበገበው በሀገረ አሜሪካ እስከ ሁለተኛ ዲግሪው ድረስ የተማረው ግርማሜ ነዋይ፣ በወቅቱ በብርጋዴል ጄነራል ማዕረግ የአፄው ስርዓት ዋነኛ ጠባቂ የነበረው የ‹‹ክብር ዘበኛ›› አዛዥ ከነበረው ታላቅ ወንድሙ መንግስቱ ንዋይ፣ የፖሊስ አዛዡ ጄነራል ፅጌ ዲቡ፣ የፀጥታ ኃላፊው ኮለኔል ወርቅነህ ገበየው እና ጥቂት ቆራጦች ያላቸውን ኃይል አስተባብረው፣ ዘራፊውን ዘውዳዊ ስርዓት በኃይል ለማስወገድ ታህሳስ 2 ቀን 1953 ዓ.ም የመፈንቅለ መንግስት ሙከራ አደረጉ፡፡ ሆኖም ሙከራው በብዙ መስዕዋትነት ቢቀለበስም፣ የለውጡን መንፈስና ይዘውት የተነሱትን ጥያቄ ግን መቀልበስ አልተቻለምና፤ ይህ ከሆነ ከ13 ዓመት በኋላ የንጉሱ ስርዓት ላይመለስ በሕዝብ ኃይል ተሰናበተ፡፡ …የእነ ግርማሜ ነዋይ ሕዝባዊ ትግል የተቀሰቀሰበት ያ ዕለትም በሀገሪቱ ታሪክ ‹‹የታህሳስ ግርግር›› በመባል በወርቅ መዝገብ ተጻፈ፡፡
ታሪክ ሊደገም ይሆን?
እነሆም በስምና በጥቂት ነገሮች ከ“ቫምፓየሩ" የአጼው ስርአት መጠነኛ ለውጥ አድርጎ ወደ ስልጣን የመጣው ኢህአዴግ መራሹ መንግስት የዲሞክራሲና የፍትሕ ጥያቄ ያነሱ ጋዜጠኞችንና ፖለቲከኞችን በዛሬው ዕለት (ታህሳስ ሁለት ቀን) ፍርድ ቤት ያቀርባል፡፡ በዚህም መሰረት ርዕዮት አለሙ ጠቅላይ ፍርድ ቤት፣ የኦፌዴንና የኦህኮ የአመራር አባላት ኦልባና ሌሊሳ እና በቀለ ገርባን ጨምሮ 29 ሰዎች በከፍተኛው ፍርድ ቤት ፣ እኔ ደግሞ በነሃሴ ወር ተቋርጦ ከቃሊቲ በነፃ በተለቀኩበት ክስ በድጋሚ በከፍተኛው ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት እንቀርብ ዘንድ ተገደናል፡፡ የታህሳስ ግርግር መንፈስ ማለትም ይህ መሰለኝ፡፡
የሆነ ሆኖ ይህ ሁሉ ንፁሐን ጋዜጠኛና ፖለቲከኛ ፍርድ ቤት የሚቀርበው የሀገሬ ጉዳይ ይመለከተኛል በሚል የመብትና የዲሞክራሲ ጥያቄ በማንሳቱ ነው፡፡ በእርግጥም በግሌ ትላንት ያነሳሁትን ጥያቄ ነገም እንደማነሳው ቃል እገባለሁ፡፡ አምኜበት እና እውነትነቱን አረጋግጬ በፍትሕ ጋዜጣ በኩል ላስተላለፍኳቸው ሃሳቦች ዋጋ መክፈል ካለብኝ ዋጋ እከፍላለሁ እንጂ የትም ልሄድ አልችልም፡፡ እናም ፍርድ ቤቱ በሀቅ የሚሰጠውን ውሳኔ በደስታ እንደምቀበለው ሁሉ፤ በትዕዛዝ የሚፈርድብኝንም የግፍ ፍርድ በፀጋ እቀበለዋለሁ፡፡
ጭቆና፣ የመብት ረገጣ፣ አምባገነን አገዛዝ፣ የሰብአዊ መብት ጥሰት፣ የሀገር ሃብት ዘረፋ፣ አድሎአዊ አስተዳደር… እስካልተወገደ ድረስ እኔም ሆንኩ ሌሎች የጠየቅነውን ጥያቄ ሚሊዮኖች እንደሚጠይቁት አምናለሁ፡፡ በዚህ ላይ ባለኝ እምነትም ነገ በፍርድ ቤት የምገኘው የቅርብ ጊዜን ተስፋ ሰንቄ ነው፡፡ በጣም የቅርብ ጊዜ፡፡ ድምፄን ከፍ አድርጌ እንዲህም እላለሁ ፤ በጣም ከፍ አድርጌ፣ ይታየኛል የሀገሬ ልጆች፣ ሴቶችና ወንዶች እጅ ለእጅ ተያይዘው ዳገቱ ላይ ሲደርሱ፡፡
ኢትዮጵያ ለዘላለም



Sunday, December 9, 2012

ጠቅላይ ሚ/ር ሀይለማርያም ኢትዮጵያ ከኤርትራ ጋር ለምታደርገው የእግር ኳስ ጨዋታ ቦታ እንዲለወጥ መጠየቁን አላውቅም አሉ
ኢሳት ዜና<

                                                                                 






--------------""ወያኔዎች ስልጣኑን ለማቆየት እንኳንስ ባድመን አዲግራትንም ስጡን ቢሉዋቸው ሰጥተው ለመደረዳር ዝግጁ ናቸው”
__________"ወያኔ ከተቃዋሚዎች ጋር መደራደር የዲሞክራሲ እና የስልጣን ጥያቄ የሚያስነሳ ነገር በመሆኑ አይፈልገውም”  < የግንቦት 7 ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ 

ኢሳት ዜና:-አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ይህን የተናገሩት ከአልጀዚራ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት
 ቃለምልልስ ነው። ረዩተር የኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ቃል አቀባይ የሆኑትን አቶ መላኩ አየለን በመጠቀስ ” ለተጫዋቾች ደህንነት ሲባል እግር ኳስ ፌደሬሽኑ የጨዋታው ቦታ እንዲቀየር መጠየቁን ” ዘግቦ ነበር። ቢቢሲና አልጀዚራን የመሳሰሉ ታላላቅ አለማቀፍ የመገናኛ ብዙሀንም ለጉዳዩ የዜና ሽፋን መስጠታቸው ይታወቃል።

በኢትዮጵያ በኩል የቀረበውን ጥያቄ ተከትሎ ኤርትራ ከኢትዮጵያ ጋር የነበራትን ጨዋታ መሰረዙዋን የአፍሪካ እግር ኳስ ኮንፌዴሬሽን መግለጹን ረዩተር ከትናንት በስቲያ ዘግቧል።

እነዚህ ዘገባዎች በስፋት በመገናኛ ብዙሀን በቀረቡበት ሁኔታ ነው፣ አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ” ከኤርትራ ጋር ወዳጅነት ከፈለጋችሁ ለምን ከኤርትራ ጋር ለምታደርጉት የእግር ኳስ ጨዋታ የመጫዎቻ ቦታው እንዲቀየር ፈለጋችሁ?” በሚል ለቀረበላቸው ድንገተኛ ጥያቄ በመደናገጥ መረጃ የለኝም ሲሉ መለስ የሰጡት።

የአንድ አገር ጠቅላይ ሚኒስትር በውጭ ፖሊሲ ዙሪያ የመጨረሻውን ውሳኔ የሚሰጥ አካል መሆኑ በህገመንግስቱ ተቀምጧል። አቶ ሀይለማርያም ትልቅ አገራዊ የመነጋጋሪያ አጀንዳ የሆነውን ጉዳይ አለውቅም ማለታቸው አንድም ውሳኔው ከእርሳቸው ውጭ በሆነ አካል የተወሰነ ነው፣ ሌላም ለቃለምልልሱ ሲቀርቡ ረዳቶቻቸው አስቀድመው እንዲዘጋጁ ባለማድረጋቸው አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትር አሻንጉሊት ናቸው የሚለውን መልእክት ሆን ብሎ ለማስተላለፍ ከእርሳቸው ጀርባ ባሉ ሰዎች የተቀነባበረ ሊሆን ይችላል” በማለት የኢሳት ዘጋቢ አስተያየቱን አስፍሯል።

አቶ ሀይለማርያም አስመራ በመሄድ ከአቶ ኢሳያስ ጋር ለመነጋገር ዝግጁ መሆናቸውንም ገልጸዋል። የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ መለስ ዜናዊም ከአቶ ኢሳያስ ጋር አስመራ በመሄድ ለመነጋገር ከ50 ጊዜ በላይ መጠየቃቸውን ተናግረዋል። የአቶ መለስ መንግስት ከኤርትራ ጋር ለመነጋገር 5 ቅድመ ሁኔታዎችን አስቀምጦ እንደነበር ይታወሳል። አቶ መለስ እነዚህ ቅድመ ሁኔታዎች ካልተሙዋሉ በስተቀር ከአቶ ኢሳያስ ጋር እንደማይነጋጋሩ በፓርላማ ፊት በተደጋጋሚ ይናገሩ ነበር። አዲሱ ጠቅላይ ሚኒስትርም ስለ5ቱ ቅድመ ሁኔታዎች ምንም አለማለታቸውን ዘገቢያችን ገልጿል።

” አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ በቅርቡ ወደ አስመራ በመሄድ ከአቶ
 ኢሳያስ ጋር ለመደራደር ፍላጎት እንዳላቸው ገልጸዋል፤ የባድሜን ጉዳይ አላነሱም። በዚህ ላይ የእርስዎ አስተያየት ምንድነው ?’” ተብለው አስተያየታቸውን የተጠየቁት የግንቦት 7 ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ ፣ “ወያኔዎች ስልጣኑን ለማቆየት እንኳንስ ባድመን አዲግራትንም ስጡን ቢሉዋቸው ሰጥተው ለመደረዳር ዝግጁ ናቸው” በማለት መልሰዋል።

ከኤርትራ ጋር ለመደራደር ከመለመን ይልቅ ቀላሉ መንገድ ከተቃዋሚዎች ጋር መደራደር አይደለም ወይ ተብለው ለተጠየቁት ደግሞ ፣ ዶ/ር ብርሀኑ ሲመልሱ ” ከተቃዋሚዎች ጋር መደራደር የዲሞክራሲ እና የስልጣን ጥያቄ የሚያስነሳ ነገር በመሆኑ አይፈልገውም” በማለት መልሰዋል

“አንዳንድ ምሁራን ‘ መንግስት ባድመን ካስረከበ ከትግራይ ህዝብና ከህወሀት ታጋይ ተቃውሞ ሊነሳበት ይችላል’ በማለት አስተያየት ይሰጣሉ ተብለው ለተጠየቁት ደግሞ ፣ ዶ/ር ብርሀኑ ” ወያኔ የትግራይን ህዝብ በሀይል እጨፈልቀዋለሁ ብሎ እንደሚያስብ እና ስልጣኑን የሚያቆይለት መስሎ ከታየው ምንም ነገር ለማድረግ ወደ ሁዋላ አይልም” በማለት መልሰዋል።

Saturday, December 8, 2012

The Voices of Oromo Women–A whisper into the Soul of Oromo Men


By Sabbontuu Jiilchaa
Introductory note  by  Ayantu Tibesso
A little over a year ago, while doing research for a term paper, I came across the following article by a woman named Sabbontuu Jiilcha. I first found an excerpt of this piece cited by John Sorenson in Ghosts and Shadows. I was greatly interested in the work and sought to learn more about the piece and the author. Upon doing further research, I was able to locate the full document online (I cannot remember where now). Unfortunately, I was only able to locate the piece and almost no information about the author. From what I have read in other places, I believe the author was a former OLF freedom fighter.
What she describes in this piece is an unfortunate predicament in which Oromo women found themselves after having fought Abyssinians alongside Oromo men in the 80s and 90s. Much to their disbelief, former women soldiers in the OLF found themselves being pushed back into the background. After what they had thought to be a fight for Oromo liberation (of both Oromo Men and women) had ended, the women found themselves fighting a different kind of battle. This piece speaks great volume of early Oromo women’s attempt to engage in an all-encompassing liberation undertakings–political, economic, social and cultural. They envisioned a liberation that would free all Oromo from shackles of both colonialism and patriarchal oppression. I will not go into further analysis as the piece eloquently captures what remains to be the reality for Oromo women. The progress made thus far, however meager, was possible because women such as Sabbontuu Jiilcha, fought vigorously for liberation of all Oromo people. We republish this piece to salute Jiilcha and call those who stand on her back to reengage in a domain that is increasingly becoming exclusive to Oromo men – the struggle for Oromo freedom



Friday, December 7, 2012

Thursday, December 6, 2012

በጉራ ፈርዳ የእርሻ መሬታችን እየተሸጠብን ነው ሲሉ ሠፋሪ አርሶ አደሮች ከሰሱ


በጉራ ፈርዳ የእርሻ መሬታችን እየተሸጠብን ነው ሲሉ ሠፋሪ አርሶ አደሮች ከሰሱ!

በቤንች ማጂ ዞን ጉራ ፈርዳ ወረዳ የሚኖሩና ከዓመታት በፊት አሁን የአማራ ክልል ከሚባለው አካባቢ የመጡ ሠፋሪ አርሶ አደሮች በአካባቢው ባለሥልጣናት ተገደው ቀያቸውን ልንዲለቁ መገደዳቸውን መዘገባችን ይታወሳል።

ከረዥም ጊዜ በፊት በአካባቢው እንዲሰፍሩ የተደረጉና አሁንም ድረስ በዚያው ነዋሪ የሆኑ አርሶ አደሮች የእርሳ መሬታችንን እንዳናርስና በማሳ ላይ የእርሻ ያለበትን ጨምሮ በሃራጅ እየተሸጠባባቸው መሆኑን ይናገራሉ ።   

የጉራ ፈርዳ ሠፋሪ አርሶ አደሮች...ዝርዝሩን ከዚህ ያዳምጡ

መለስ ከመቃብር እየገዙ ነው። ግን እስከመቼ ይዘልቅ ይሆን?

መለስ ከመቃብር እየገዙ ነው። ግን እስከመቼ ይዘልቅ ይሆን?” የሚል ፅሁፍ አስነብበዋል፡

ከሠሃራ በስተደቡብ ያሉ የአፍሪካ ሃገሮችን በተመለከተ በሚያደርጓቸው ምርምሮችና ዘገባዎች በዋናነት ከሚታወቁት ተንታኞች አንዱ የሆኑት 
ሬኔ ለፎር

ሬኔ ለፎር ከቪኦኤ የአፍሪካ ቀንድ ኃላፊ ፒተር ሃይንላይን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ሰሞኑን የተሰጠውን ሦስት የምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሮች እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሹመት ይገመግማሉ፡
----<<<በአስተዳደሩ ውስጥ የትግራይ ተወላጆች የመንግሥቱን ሥልጣን እንደገና እየተቆጣጠሩ ናቸው
በማለት ያብራሩበትንና ተዛማጅ ጥያቄዎችን የመለሱበትን