Sunday, December 29, 2013

ፍትህ የተጠማች ብላቴና


ፍትህ የተጠማች

አሳዛኝ ግፍ የስምንት አመቷ ስለእናት ማስረሻ ቀኝ እጇ ላይ በጥይት ተመታች፡፡ባለቤታቸውን በሞት የተነጠቁትና ምንም የማታውቀውን ህጻን ልጃቸውን አካለ ጎደሎ ያደረገባቸውን ጥይት ማን እንደተኮሰው ለማወቅ ለዳባት ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ አቤት ሲሉ ‹‹ባለቤትዎ ሽፍታ እንደሆኑ መረጃ ስለደረሰን ግድያውን የፈጸመው የጸረ ሽብር ግብር ሃይል ነው››ተብለዋል፡፡ ‹‹ሽፍታ እንዴት ባለ80 ቆርቆሮ ቤት ይሰራል? ልጆቹን ያስተምራል? ሞዴል አርሶ አደር ተብሎ ይሸለለማል? በየት አገር በብአዴን ስብሰባ ላይ እንድትገኝ ተብሎ በደብዳቤ ይጠራል? እንዴት ሽፍታ የመለስ ዜናዊን አደራ ለመወጣት በምንችልበት ሁኔታ ለመወያያት እንድንነጋገር ይባላል? ›› ጥያቄዎቹን ፖሊሶቹ ሊመልሱላቸው ባለመቻላቸው ወደ ክልሉ አስተዳደር አምርተዋል፡፡ክልሉ ለዞኑ ዞኑ ለወረዳው ደብዳቤ እየጻፈ እስካሁን ድረስ የአቶ ማስረሻ እውነተኛ የግድያ መንስኤ መታወቅ አልቻለም፡፡ ይህች ህጻንና ቤተሰቦቿ የሁላችሁንም ወገንተኝነት በአክብሮት ይጠይቃሉ ሰሜን ጎንደር ዳባት ወረዳ ነዋሪ የነበሩት የ55 ዓመቱ አቶ ማስረሻ ጥላሁን የተመሰከረላቸው አርሶ አደር ገበሬ በመሆናቸው የክልሉ ግብርና ጽ/ቤት ሞዴል አርሶ አደር በማለት ሸልሟቸዋል፡፡የሁለት ወንድና የአምስት ሴት ልጆች አባት የሆኑት አቶ ማስረሻ ወሰኔን ገፍተሃል የሚል ክስ ቀርቦባቸው በዳባት ፍርድ ቤት 300 ብር መቀጮ ተጥሎባቸው በመክፈል ወደ እርሻቸው ቢመለሱም የገበሬ ቀበሌ ማህበሩ ሊያስቀምጣቸው አልቻለም፡፡ ጥቅምት 15/2006ዓ.ም ከሁለተኛ ልጃቸው ሰለሞን ማስረሻ ጋር አትክልት ተክለው አመሻሹ ለይ ተዳክመው መኖሪያ ቤታቸው ገብተዋል፡፡ማለዳ 12፡00 ከመኝታው ባላቋረጠው የውሾች ጩህት ከእንቅልፉ ተነሳው ሰለሞን በሩን ከፍቶ ሲወጣ የጥይት እሩምታ ይወርድበታል፡፡አባት ልጄን ብለው የሌሊት ልብሳቸውን እንደለበሱ ወደ ውጪ ሲወጡ የጥይቶቹ አቅጣጫ ወደ እርሳቸው በመዞሩ ማን እንደተኮሰባቸውና ማን እንደመታቸው ለማየት እንኳን ሳይታደሉ ይህችን ጨካኝ አለም ተሰናበቱ፡፡ መኖሪያ ቤቱ ላይ በሚወርደው የጥይት እሩምታ የተነሳ ሁለት ላሞችና አንዲት ጊደር ተገደሉ፡፡የስምንት አመቷ ስለእናት ማስረሻ ቀኝ እጇ ላይ በጥይት ተመታች፡፡



Tuesday, December 24, 2013

የሰው ህይወት ከዱር እንሰሳ ያነሰበት!!!!

>>>የሰው ህይወት ከዱር እንሰሳ ያነሰበት!


ኣብዛኞቹ ኦሮሞ የሆኑ የተለያዩ ብሄር ብሄረሰብ ተወላጆች ባገራቸው ሰርተው ማደግ ተስኖኣቸው በያመቱ ወደ ጎርቤትና ሩቅ ሃገራት ይሰደዳሉ። ኣብዛኞቹ በህገ ወጥ መንገድ ድንበር ኣሳብረው ጎሮቤት ኣገራት ይገባሉ። ጎሮቤት ኣገራቱ ውስጥም የወያኔ መንግስት ተጽእኖ ኣላሰራ ሲላቸው ለደህንነታቸው ሰግተው ርቀው ለመሄድ ሲሉ የከፋ ኣደጋ ያጋጥማቸዋል። በዚህ ሁኔታ በሱዳን፣ ሶማሊያ፣ ሶማሊ ላንድ፣ ፑንት ላንድ፣ ጅቡቲ፣ ኬንያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ የመን፣ ሳውዲ ኣረቢያ፣ ዱባይ፣ ባህሬን፣ ሊባኖስ፣ ቃታር፣ ግብጽ እና ደቡብ ኣፍሪካ በመሳሰሉት ኣገራት ውስጥ ተሰድደው የሚገኙ ከኦሮሞና ከሌሎችም ብሄር ብሄረሰብ የሆኑ ዜጎች ብዛት በመቶ ሺዎች የሚገመት ነው።
ከነዚህ ስደተኞች አብዛኞቻችን በፖለቲካ ችግር ሳቢያ የሚወዷትን ኣገራቸውን ለቀው የወጡ ናቸው። የተቀሩትም ባገራቸው ሰርተው የመለወጥና ራሳቸውን ችለው ቤተሰቦቻቸውን የመደገፍ እድል ተነፍገው በፖለቲካ ኣመለከከታቸዉ አነ በዘረቸው ምከነያት በደረሰበቸው ግፉ ርቀው የሄዱ ናቸው። ባገራቸው ነግደው፣ ኣርሰው፣ ኣርብተው ኣልያም ባላቸው ሞያ ኣገልግለው እንዳይለወጡ ስልጣን ላይ ያለው ስርኣት እንቅፋት ሆነባቸው። የወያኔ መንግስት ባገራቸው ከማናቸውም መንግስታዊ የፖለቲካ ጉዳዮች ነጻ ሆነው ሰርተው መሻሻል የሚፈልጉትን ዜጎች የግድ የፓርቲዬ ኣባል ካልሆናችሁ እያለ ያስፈራራቸዋል። ይህን የማይቀበሉትን በሰበብ ኣስባቡ ኣደናቅፎ የስራ እድል ይዘጋባቸዋል። ኣርሶ ኣደሮቹን የማዳበሪያና የምርጥ ዘር ዋጋ ያስወድድባቸዋል ኣልያም ከናካቴው ይከለክላቸዋል። ነጋዴዎቹን ውሃ ቀጠነ ብሎ በማስቸገር የንግድ ፈቃዳቸውን ከነጠቀ በሁዋላ ይህን ያህል ሺ ገንዘብ ካልከፈልክ ኣታገኝም ይላቸዋል። ወደ ንግዱ ኣለም ለመግባት ያላቸውን ሃብት ኣስይዘው ከባንክ ገንዘብ መበደር የሚፈልጉትን በቅድሚያ የፓርቲያችን ኣባልነት መታወቂያ ኣምጣ በማለት ያሰናክላቸዋል። እነዚህ እንቅፋቶች ዜጎች ባገራቸው ሰርተው ራሳቸውንም ሆነ ኣገራቸውን እንዳያሳድጉ በማደናቀፍ ልባቸው ስደት እንዲመኝ ገፋፉ። ከኢትዮጵያ እየወጡ ወደተለያዩ ኣገራት ስራ ፍለጋ የተሰደዱ ዜጎች ቁጥር ከማናቸውም የጎሮቤቶቻችን ኣገሮች ልቆ የሚገኝበት ምክንያትም በዚህ ኣይነቱ የመንግስት ተጽእኖ ሳቢያ ነው ቢባል ማጋነን ኣይሆንም።
እነዚህ ስራ ፍለጋ የሚንከራተቱ ዜጎች የኢትዮጵያ ዜጎች እስከተባሉ ድረስ በደረሱበት ሁሉ ደህንነታቸውን የመከታተል ሃላፊነት የወደቀው ኣገር መሪ ነኝ በሚለው የወያኔ መንግስት ጫንቃ ላይ ነው። የወያኔ ህወሃት መንግስት ግን በኣንጻሩ ስደተኞቹ በደረሱባቸው ኣገራት ለሰብኣዊ ፍጡር የማይገቡ የጭካኔ እርምጃዎች ሰለባ እንዲሆኑ በማድረጉ ሴራ ውስጥ በቀጥታም ባይሆን በተዘዋዋሪ ተሳታፊ መሆንን መረጠ። በተለያዩ ጊዜያት ዜጎች ለስራ ፍላጋ በተሰደዱባቸው ኣገራት ተገድለው ሬሳቸው ጎዳና ላይ ሲጣል፣ ደማቸው እንደ ውሻ ደም የትም ሲፈስ ወያኔ ይህ ለምን ሆነ ብሎ ሲጠይቅ ኣልተሰማም።
ሰርተው ለመቀየር ያለሙ የኣገራችን ሴቶች ለግርድና ስራ ወደ ኣረብ ኣገራት ተሰድደው በጭካኔ ሲገደሉ፣ ሲደፈሩና ያፈሩትን ጥሪት ሲነጠቁ በተደጋጋሚ ተሰምቷል። ኣንዳንዶቹ ምሬት ጠንቶባቸው ከፎቅ ላይ ራሳቸውን ወርዉረው ነፍሳቸውን እንዳጠፉም ይታወቃል። ከኣንድ ኣመት ገደማ በፊት ኣለም ደቻሳ የተባለች የኦሮሞ ተወላጅ በቤይሩት ጎዳና ላይ በኣገሬው ሰዎች እንደ እባብ ስትቀጠቀጥ የሚያሳይ ቪድዮ በ ዮቲዩብ መለቀቁ ይታወሳል። ኣለም በወቅቱ እነዚያ ኣረመኔ የኣረብ ወጣቶች የሴትነት ክብሯን ደፍረው እርቃኗን ጎዳና ለጎዳና እየጎተቱ ሲጫወቱባት እዚያ ኣገር የሚገኘው የወያኔ ኤምባሲ እንዲደርስላት እያለቀሰች ስትማፀን በዚያው ቪድዮ ላይ ተስምታለች። ኤምባሲው ግን ኣልደረሰላትም። የሚገርመው ደግሞ ኣለም ደቻሳ ላይ እንዲህ ያለው ዘግናኝ በደል የደረሰው የወያኔ ኤምባሲ ካለበት ሁለት መቶ ሜትሮች ብቻ ርቆ በሚገኝ ስፍራ ላይ መሆኑ ነው። የወያኔ መንግስት በዚህ ኣንገብጋቢ ጉዳይ ላይ የኣገሪቷን መንግስት የጠየቀው ነገር ኣልተሰማም።
በቅርቡም እንደሚታወቀው ሳዉዲ ኣረቢያ ውስጥ በስራ ላይ ተሰማርተው ይኖሩ በነበሩ የኢትዮጵያ ዜጎች ላይ ኣስነዋሪ የጭካኔ እርምጃዎች ለሳምንታት ሳይቁዋረጡ እየተወሰዱ ናቸው። በዚህም እርምጃ ቢያንስ የሶስት ዜጎች ህይወት ጠፍቷል። የሳውዲ ፖሊሶች ከኣገሬው ወጣቶች ጋር በመሆን ዜግነታቸው ከኢትዮጵያ በሆነ ስድተኞች ላይ የተለየ ኣስነዋሪ የጭካኔ ድርጊት ሲፈጽሙ በተቀረጸው የቪድዮ ምስል ታይተዋል። ይህ ሁሉ ሲሆን እነዚህ የሚደበደቡ፣ የሚገደሉና የሚደፈሩ ዜጎች የትውልድ ኣገር መንግስት የሆነው ወያኔ ኣፉን ሞልቶ ድርጊቱን ሲያወግዝ ኣልተሰማም።
እንደ ኢንዶኔዢያና ፊሊፒንስ ያሉ መንግስታት ዜጎቻቸው ከሳውዲ በሃይል መፈናቀላቸውን ተቃውመው ወዲያውኑ የቅሬታ መግለጫ በማውጣት የሳውዲን መንግስት ኣወገዙ። በሳውዲ የሚኖሩትን የሃገራቸው ስደተኛ ዜጎች ደህንነት ለማስጠበቅ ባላቸው ኣቅም ሁሉ እርምጃ ወሰዱ። የወያኔ መንግስት ግን እንዲህ ያለውን መንግስታዊ ሃላፊነት መወጣት ቀርቶ እንዲያውም የሳውዲን መንግስት ጸረ ሰብኣዊ መብት እርምጃ ለመደገፍ እየተሞዳሞደ መሆኑን በራሱ ላይ መስከረ። በኣገሩ ዜጎች ላይ ሳውዲ ውስጥ እየደረሰ ላለውና ኣለምን እያሳዘነ ለሚገኘው ውርደት ስሜት ኣልነበረውም። ወያኔ ዘንድ ዋጋ የሚያወጣው ለኣገሩ ዜጎች ክብር መቆም ሳይሆን ለሳውዲ ኢንቨስተሮች መሬት ሸጦ ኣልያም በነጻ ሸንሽኖ እየሰጣቸው በኣጸፋው በሚወረወርለት ጥቅማ ጥቅም የንዋይ ጥማቱን ማርካት ብቻ ነው። ዜጎች ኣገራቸው ላይ ሰርተው እንዳያድጉ በሰበብ ኣስባቡ ገፍቶ በማስወጣት እነርሱ ለቀው የሄዱለትን መሬት ዛሬ ዜጎቹን እየገደሉ ላሉት የኣረብ ጥጋበኞች ይቸበችባል። ይህ የኣንድ ጸረ ህዝብ መንግስት ትልቁ መለያ ምልክት ነው።
እንደ ሱዳን፣ የመን፣ ጅቡቲ፣ ሶማሊ ላንድ፣ ፑንት ላንድ፣ ኬንያና በመሳሰሉት ሃገራት ውስጥ ከረጅም ጊዜ በፊት ጀምሮ ከኢትዮጵያ በሄዱ ዜጎች ላይ የሚደርሰው የሞትና እንግልት ኣደጋ ተነግሮ የሚያልቅ ኣይደለም። ይህ ሁሉ ሲሆን ታዲያ የወያኔ መንግስት ከነዚያ የባእድ መንግስታት ጋር ተባብሮ ስደተኞቹን ማስገደል፣ ማሳሰርና ወደ ሃገር ቤት መልሶ ማሰቃየት ካልሆነ በስተቀር ዜጎቼ ብሎ ደርሶላቸው ኣያውቅም።
በጥቅሉ ሲታይ በባእድ ኣገራት ውስጥ በኦሮሞና ሌሎችም ብሄር ተወላጅ ስራ ፈላጊ ስደተኞች ላይ እየደረሰ ላለው ሰቆቃ ዋነኛ ተጠያቂው ባእዳኑ መንግስታት ሳይሆኑ ራሱ የወያኔ መንግስት ነው። በበርካታ ምክንያቶች ተጠያቂ ይሆናል። በመጀመሪያ ደረጃ ስደተኞቹን ገፍቶ ከሃገር እንዲወጡ በማድረጉ ይጠየቃል። በሁለተኛ ደረጃ ስደተኞቹ በደረሱባቸው ኣገራት ሰብኣዊ መብታቸው ተከብሮ እንዲሰሩ በኤምባሲዎቹ ኣማካኝነት ክትትል ባለማድረጉ ተጠያቂ ይሆናል። ሶስተኛ ደግሞ ስደተኞቹ በሚኖሩባቸው ኣገራት ሰብኣዊ መብቶቻቸውን ሲገፈፉ ፈጥኖ ደርሶላቸው ተገቢውን እርምጃ ኣለመውሰዱ ተጠያቂ ያደርገዋል።
ከሁሉም በላይ ግን ስራ ፈላጊዎቹ ዜጎች በገዛ ኣገራቸው ላይ ሰርተው ራሳቸውን እንዲችሉ በማበረታታት ምትክ ተስፋ ቆርጠው ስደትን እንዲመርጡ መገፋፋቱ ትልቅ መንግስታዊ ጉድለት ነው። ዜጎቹ ኣገራቸውን ለቀው ኣንዳይሄዱ ለማድረግ ከፖለቲካ ተጽእኖ ነጻ የሆነ የስራ እድል ማመቻቸት መንግስታዊ ሃላፊነቱ ነበረ። ሁሉም ዜጎች በሚኖሩባቸው ክልሎች ከማናቸውም የፖለቲካ ኣመለካከቶች ነጻ የሆነ ሰርቶ የመሻሻል እድል ማግኘት መብታቸው ነበር። ወያኔ ያንን የዜግነት መብታቸውን ቀማ። ለምሳሌ የኦሮሞ ተወላጆች በክልላቸው ኦሮምያ ውስጥ ባለው የተፈጥሮ ሃብት ተጠቅመው ሰርተው መሻሻል ይችሉ ነበር። በእርሻ፣ በከብት ርቢ፣ በንግድ እንዲሁም በሲቪል ኣገልግሎቶች መንግስታዊና መንግስታዊ ባልሆኑ መዋቅሮች ውስጥ ያላንዳች የፖለቲካ ተጽእኖ ተሰማርተው ራሳቸውንም ሆነ ኣገራቸውን መጥቀም ይችሉ ነበር። የወያኔ መንግስት ግን እነዚህን መሰል የስራ እድሎች ነጥቆኣቸው ለስደት ህይወት ዳረጋቸው። በስመ እንቬስተርነት የራሱን ካድሬዎችና ሰላዮች መልምሎ በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ኣሸክሞ ክልሎች ላይ በማሰማራት የስራ እድሉን ነጠቃቸው።
የዚህ ችግር መንስኤ ራሱ የወያኔ መንግስት ኣድሎኣዊ ኣሰራር እስከሆነ ድረስ የችግሩ መፍትሄም በራስ ኣገር ላይ ሰርቶ የመኖርን መብት የቀማውን ስርኣት ታግሎ የራስን መብት ማስከበር ብቻ ነው። የነዚህ ስራ ፈላጊ ስደተኞች ችግር ላይ ላዩን ሲታይ የኢኮኖሚ ችግር ይምሰል እንጂ መሰረቱ ግን ኣገር ቤት ላይ የሚደርሰው የፖለቲካ ጫና መሆኑ ታውቆ የፖለቲካ መፍትሄ ሊያገኝ ይገባል። ጎሮቤት ኣገራትና መካከለኛው ምስራቅ ውስጥ ስራ ፍለጋ ሲንከራተቱ የተገደሉ፣ የተደበደቡ፣ ለኣካል ጉድለት የተዳረጉ፣ የታሰሩና በሃይል ተይዘው ወደ ኣገራቸው የተመለሱ የኦሮሞና ሌሎች ብሄሮች ተወላጅ የሆኑ ዜጎች በሙሉ ራሳቸውን መጠየቅ ያለባቸው ጥያቄም ይሄው ነው። ኦሮምያ ላይ ሌላው ሰርቶ በኣጭር ጊዜ ውስጥ ሚሊዮነር ሆነ ሲባል እኔ ለምን ኣገሬ ላይ ሰርቼ ማደግ ተሳነኝ? ለምን ለስደት ህይወት ተጋልጬ በባእድ ኣገር ላይ ተዋረኩ? የሚሉትን ጥያቄዎች ራሳቸውን ጠይቀው ምላሹንም ማግኘት ይገባቸዋል።

Saturday, December 21, 2013

ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን በማሰር ከዓለም 2ኛ ሆነች!!!







መቀመጫውን በኒዮርክ ያደረገው የጋዜጠኞች መብት ተቆርቋሪ ቡድኑ /CPJ/  ባለፈው ረቡዕ  ይፋ ባደረገው ሪፖርት፤ ጋዜጠኞችን በማሰር ከአለም አስር አገሮች መካከል ኢትዮጵያን በሁለተኛ ደረጃ ያስቀመጠ ሲሆን ኤርትራ ቀዳሚ ሆና፣ ግብፅ በሶስተኝነት ተቀምጣለች፡፡ 
ሲፔጂ 34 አፍሪካዊ ጋዜጠኞች በሰሜንና ምስራቅ አፍሪካ በእስር ላይ እንደሚገኙ የገለፀው ሲፒጄ፤ በኢትዮጵያ ሰባት ጋዜጠኞች በጻፉት ጽሑፍ ሣይሆን “አሸባሪ” ተብለው በእስር ላይ እንደሚገኙ ጠቁሟል፡፡ 
አለም አቀፍ የመብት ቡድን (Global rights group) የተባለው ተቋም በበኩሉ፤ የኢትዮጵያ መንግስት ጋዜጠኞቹን ያሰራቸው ሚዲያውን ዝም ለማሰኘት ስለሚፈልግ ነው ብሏል። በኤርትራ 22 ጋዜጠኞች በእስር ላይ እንደሚገኙና አንዳቸውም ፍርድ ቤት እንዳልቀረቡ የገለፀው ሲፒጄ፤ እስረኞቹን በተመለከተ ከኤርትራ መንግስት ምንም አይነት መረጃ ለማግኘት እንደተቸገረ ጠቁሟል፡፡ ጋዜጠኞችን በማሰር የ3ኛ ደረጃን በያዘችው ግብፅም ጋዜጠኞች መታሰር የጀመሩት ፕሬዚዳንት መሀመድ ሙርሲ ወደ ስልጣን ከመጡበት ቀን ጀምሮ ነው ብሏል ሲፒጄ፡፡ የሰሜን ምስራቅ አፍሪካ ጋዜጠኞች ተወካይ ቶም ሮዲስ በናይሮቢ ለCPJ እንደተናገረው፤ በአፍሪካ ቀንድ አገራት የተለያዩ ችግሮች እንዳሉና መንግስታት ስለ ችግሩ መወያየት እንደማይፈልጉ ገልጿል፡፡ ሲፒጄ ጋዜጠኞችን በማሰር ቀዳሚዎቹ 10 አገራት በሚል ከዘረዘራቸው መካከል ቬትናም፣ ሶሪያ፣ ፓኪስታንና ቤልጂየም ይገኙበታል፡፡

Tuesday, December 10, 2013

ዓለም ማንዴላን ተሰናበተች!








ማክሰኞ፣ ታኅሣስ 1/2006 ዓ.ም በደቡብ አፍሪካ በብዙ አሥር ሺሆች የተቆጠረ ህዝብ ዕኩልነትን ዕውን ለማድረግ አስቸጋሪ የሆነ የረጅም ጊዜ ትግል ያካሄዱትን የፀረ-አፓርታይድ ትግል መሪውን ኔልሰን ማንዴላን ተሰናብቷል።

በጆሐንስበርግ ሶከር ሲቲ ስታዲየም የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ባራክ ኦባማንና የቀደሙ የአሜሪካ ፕሬዚዳንቶችን ጨምሮ በርካታ ታላላቅ ዕንግዶች፣ ታዋቂ ሰዎች እና ደቡብ አፍሪካዊያን መጥፎ የአየር ሁኔታ ሳይበግራቸው እኒህን ሁሉ ሰው ”ታታ” እያለ በፍቅር የሚጠራቸውን ሰው በአክብሮት ለመሰናበት ተገኝተዋል

Sunday, December 8, 2013

የደህንነት አባሉ ተጨማሪ 11 ክሶች ቀረበባቸው!



<<>>>በርካታ ድርጅቶች በሽብር ላይ የሚያተኩር መጽሐፋቸውን በተጽዕኖ እንዲገዟቸው አድርገዋል
>>>>>ከቤተሰቦቻቸው ጋር በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብና ሃብት አፍርተዋል
>>>>>ሁለተኛ ተከሣሽ ደግሞ በመከላከያ ውስጥ ተቀጥሮ ሲሠራ ደሞዙ 523 ብር ሆኖ ሳለ፣ በ3 የንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ከ150 ሺ እስከ 2 ሚሊዮን ብር ሲያንቀሳቀስ እንደነበር ተመልክቷል

ከቤተሰቦቻቸው ጋር በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብና ሃብት አፍርተዋል የቀድሞው የደህንነት አባልና የትግራይ ልማት ማህበር የቦርድ ሰብሳቢ አቶ ወልደስላሴ ወልደሚካኤል፤ ከቤተሰባቸው ጋር በመሆን ፈጽመውታል በተባለው የሙስና ወንጀል ተጨማሪ 11 ክስ ቀረበባቸው፡፡ ግለሰቡ ከእነ አቶ መላኩ ፈንታ ጋርም በሌላ መዝገብ መከሰሳቸው ይታወሣል፡፡ አቶ ወልደስላሴ፤ አሁን ለተጨማሪ ክስ የዳረጋቸውን ወንጀል ፈፀሙ የተባለው የብሔራዊ መረጃና ደህንነት አገልግሎት መ/ቤት ሠራተኛ በነበሩበት ጊዜ ሲሆን ከፊሉን ከወንድማቸው አቶ ዘርአይ ወ/ሚካኤል፣ ከእህታቸው ወ/ሮ ትርሃስ ወ/ሚካኤል እንዲሁም ከቅርብ ጓደኛቸው አቶ ዳሪ ከበደ ጋር በመመሳጠር፣ ከፊሉን ለብቻው እንደፈፀሙ ተገልጿል፡፡ ከትናንት በስቲያ ክሣቸው በንባብ የተሰማው አቶ ወልደስላሴ፤ በ1ኛነት የቀረበባቸው ክስ፤ የደህንነት መስሪያ ቤት ባልደረባ መሆናቸውን መከታ በማድረግ፣ በ2002 ዓ.ም “Terrorism in Ethiopia and the Horn of Africa” የተሰኘ መጽሐፋቸውን፣

ከመንግስት የልማት ድርጅቶች ተቆጣጣሪ ኤጀንሲ ዋና ዳይሬክተር አቶ በየነ ገ/ስላሴ ጋር ያላቸውን መልካም ግንኙነት በመጠቀምና ግለሰቡን በማታለል፣ ኤጀንሲው በሚያስተዳድራቸው ብርሃንና ሠላም ማተሚያ ድርጅት፣ ቦሌ ማተሚያ ድርጅት እና አርቲስቲክ ማተሚያ ድርጅት ስፖንሰር አድራጊነት፣ 3ሺህ መጽሐፍት በ124,000 ብር እንዲታተሙ አስደርገው በመሸጥ ገንዘቡን ለግል ጥቅማቸው አውለዋል ይላል፡፡ በዚያው ክስ ላይ በ2ኛነት የቀረበው ክስ ደግሞ፤ ግለሰቡ በዚያው አመት ይህንኑ መጽሐፍ 10ሺህ ኮፒ ለማሳተም በሚል የመጽሐፉ ይዘት ከቴሌኮሙኒኬሽን ጋር ባልተገናኘበት እና የማስተዋወቅ ስራም ባልተሠራበት ሁኔታ የደህንነት አባልነታቸውን መከታ በማድረግ ከወቅቱ የቴሌኮምኒኬሽን ሃላፊ አቶ አማረ አምሣሉ ከ385ሺ ብር በላይ መቀበላቸውን ይጠቁማል፡፡

በዚሁ ክስ ላይ በ3ኛ እና በ4ኛነት በቀረቡት ክሶች፤ ግለሰቡ በኢትዮጵያ አትክልትና ፍራፍሬ ገበያ አክሲዮን ማህበር እንዲሁም በሙገር ሲሚንቶ ኢንተርፕራይዝ የነበራቸውን የቦርድ አባልነት እንዲሁም የደህንነት ሠራተኛነታቸውን መከታ በማድረግ፣ የአክሲዮን ማህበራቱ 310 መጽሐፍትን በ62ሺ ብር እንዲገዙ ካስደረጉ በኋላ፤ ገንዘቡንም መጽሐፍቱንም ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸው ተጠቅሷል፡፡ በመዝገቡ በ2ኛነት የቀረበውም ክስ ደግሞ ግለሰቡ የደህንነት ሠራተኛ መሆናቸው የፈጠረላቸውን ተሠሚነት እንደመልካም አጋጣሚ በመውሰድ፣ ወደ 26 የሚሆኑ ኩባንያዎችና ባለሀብቶች የተለያየ ብዛት ያላቸውን መጽሐፍት እንዲገዙ ካስደረጉ በኋላ፣ መጽሐፍቶቹን ሳያስረክቡ ለግል ጥቅማቸው አውለዋል ይላል፡፡ ከእነዚህ መካከል የአልሣም ኃላ.የተ.የግ ማህበር ባለቤት አቶ ሣቢር አረጋው፤ ያለፍላጐታቸው በሌላ መዝገብ ክስ በቀረበባቸው በአቶ ገብረዋህድ ወ/ጊዮርጊስ እና በባለሀብቱ በአቶ ነጋ ገ/እግዚአብሔር በኩል 500 መጽሐፍትን በመቶ ሺህ ብር እንዲገዙ ካስደረጉ በኋላ መጽሐፍቱን ለግላቸው አስቀርተው መጠቀማቸው፣ ጌታስ ትሬዲንግ 1500 መጽሐፍትን፣ ነፃ ፒኤልሲ 700፣ ካንትሪ ትሬዲንግ 300፣ ሐበሻ ካፒታል ሠርቪስ 50፣ አኪር ኮንስትራክሽን 100 መጽሐፍትን እንዲሁም በርካታ ድርጅቶችና ግለሰቦች የተለያየ ብዛት ያላቸውን መጽሐፍት እንዲገዙ ካደረጉ በኋላ፣ መጽሐፍቶቹን ሳያስረክቡ ለግል ጥቅማቸው ማዋላቸው ተመልክቷል፡፡

በግለሰቡ ላይ በ3ኛነት በቀረበው ክስ፣ የተሰጣቸውን ሃላፊነት ያለአግባብ በመጠቀም በመዝገቡ ስሟ የተጠቀሰን ግለሰብ በመንግስት መኪና ቁልቢ ድረስ እንድትሄድና በተለያየ ጊዜ እንድትዝናና አስደርገዋል እንዲሁም ግለሰቧ ለነበረባት የፍትሃብሔር ክርክር የመ/ቤቱን ሠራተኛ መድበው፣ መደበኛ ስራውን ትቶ እንዲከታተል አስደርገዋል ይላል፡፡ በ4ኛ እና በ5ኛነት የቀረቡባቸው ክሶችም፤ ስልጣናቸውን መከታ በማድረግ፣ አቶ ሣቢር አርጋው የተባሉት ባለሃብት ጋ በመደወል፣ ለሚሠሩት ቤት ሴራሚክ እንደጐደላቸው በመንገር፣ ግለሰቡ በ65ሺህ ብር እንዲገዙላቸው ማስደረጋቸው እንዲሁም ከመጽሐፍቶቹ ሽያጭ መንግስት ይፈልገው የነበረውን ከ496ሺህ ብር በላይ ግብር አሳውቀው አለመክፈላቸው በአቃቤ ህግ የክስ ዝርዝር ላይ ቀርቧል፡፡ ቀሪዎቹ ክሶች ከቤተሰብ አባላቱ ጋር ተጣምረው የቀረቡ ሲሆን በመዝገቡ ከ6ኛ እስከ 9ኛ ክስ ሆኖ የቀረበው፣ አቶ ወልደስላሴ፤ 2ኛ ተከሣሽ የሆኑትን ወንድማቸው አቶ ዘርአይን የመኖሪያ ቤታቸው ወኪል በማድረግ፣ ቤቱ ከመኖሪያ ቤት ውጪ ለሆነ አገልግሎት እንዲውል ካደረጉ በኋላ፣ መንግስት ይፈልገው የነበረውን ከ126ሺ ብር በላይ ግብር በተገቢው መንገድ አሳውቀው አልከፈሉም፤ በዚህም የሃሰት ወይም አሳሳች መረጃ በማቅረብ ወንጀል ተከሰዋል ይላል፡፡ በተጨማሪም ከ119ሺ ብር በላይ የተርን ኦቨር ታክስ ግብርም አልከፈሉም ተብሏል፡፡

በሁሉም ላይ የቀረቡት ቀሪዎቹ ክሶች ምንጩ ያልታወቀ ሃብት ይዞ መገኘት የሚሉ ናቸው፡፡ 1ኛ ተከሣሽ ለወንድም እና እህቶቹ እንዲሁም ለቅርብ ጓደኛው ውክልና እየሰጡና ንብረትን በማስተላለፍ ዘዴ እየተጠቀሙ ሃብት አፍርተዋል ይላል፡፡ ምንጩ ያልታወቀ ሃብት ተብለው ከተጠቀሱት መካከልም በአቶ ወልደስላሴ እና በባለቤታቸው ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አምስት የተለያዩ ቅርንጫፎች ከ9ሺ እስከ 1 ሚሊዮን 5 መቶ ሺ ብር በማስቀመጥና በማንቀሳቀስ ሲጠቀሙ እንደነበር ተመልክቷል፡፡ ይህ ሲሆን የግለሰቡ ደሞዝ ከ1600 እስከ 6ሺህ ብር ነበር ብሏል አቃቤ ህግ፤ ሁለተኛ ተከሣሽ ደግሞ በመከላከያ ውስጥ ተቀጥሮ ሲሠራ ደሞዙ 523 ብር ሆኖ ሳለ፣ በ3 የንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ከ150 ሺ እስከ 2 ሚሊዮን ብር ሲያንቀሳቀስ እንደነበር ተመልክቷል፡፡ ምንም የገቢ ምንጭ እንደሌላት የተገለፀው እህቱ እና ጓደኛውም በውክልና እና በማስተላለፍ ሂደቶች የእርሻ ልማት ኢንቨስትመንት እና በአዲስ አበባ፣ በመቀሌ እና በአክሱም ቦታ እና ቤት፣ እንዲሁም በባንክ የተለያየ መጠን ያለው ገንዘብ አስቀምጠው መገኘታቸው በአቃቤ ህግ የክስ ዝርዝር ተቀምጧል፡፡ በእለቱ ክሣቸውን ፍ/ቤቱ በንባብ ካሠማ በኋላ፣ 3ኛ እና 4ኛ ተከሣሽ ያቀረቡትን የዋስትና ጥያቄ የአቃቤ ህግን መልስ መነሻ በማድረግ ውድቅ ካደረገ በኋላ፣ ተከሣሾች የሚያቀርቡትን መቃወሚያ ወይም መከራከሪያ ለመጠባበቅ መዝገቡን ለታህሣስ 7 ቀን 2006 ዓ.ም ቀጥሯል፡፡

Friday, November 29, 2013

Ethiopia most restrictive Sub Saharan Country, Freedom House reports 2013

Ethiopia most restrictive Sub Saharan Country, Freedom House reports 2013

NOV 29,2013
Ethiopia has one of the lowest rates of internet and mobile telephone penetration in the world, as meager infrastructure, a government monopoly over the telecom sector, and obstructive telecom policies have notably hindered the growth of information and communication technologies (ICTs) in the country. Despite low access, the government maintains a strict system of controls over digital media, making Ethiopia the only country in Sub-Saharan Africa to implement nationwide internet filtering. Such a system is made possible by the state’s monopoly over the country’s only telecom company, Ethio Telecom, which returned to government control after a two-year management contract with France Telecom expired in December 2012. In addition, the government’s implementation of deep-packet inspection technology for censorship was indicated when the Tor network, which helps people communicate anonymously online, was blocked in mid- 2012.

Internet Freedom

Prime Minister Meles Zenawi, who ruled Ethiopia for over 20 years, died in August 2012 while seeking treatment for an undisclosed illness. Before his death was officially confirmed on August 20th, widespread media speculation about Zenawi’s whereabouts and the state of his health prompted the authorities to intensify its censorship of online content. A series of Muslim protests against religious discrimination in July 2012 also sparked increased efforts to control ICTs, with social media pages and news websites disseminating information about the demonstrations targeted for blocking. Moreover, internet and text messaging speeds were reported to be extremely slow, leading to unconfirmed suspicions that the authorities had deliberately obstructed telecom services as part of a wider crackdown on the Ethiopian Muslim press for its coverage of the demonstrations.

In 2012, legal restrictions on the use and provision of ICTs increased with the enactment of the Telecom Fraud Offences law in September,1 which toughened a ban on certain advanced internet applications and worryingly extended the 2009 Anti-Terrorism Proclamation and 2004 CriminalCode to electronic communications.2 Furthermore, the government’s ability to monitor online activity and intercept digital communications became more sophisticated with assistance from the Chinese government, while the commercial spyware toolkit FinFisher was discovered in Ethiopia in August 2012.

Repression against bloggers, internet users and mobile phone users continued during the coverage period of this report, with at least two prosecutions reported. After a long trial and months of international advocacy on behalf of the prominent dissident blogger, Eskinder Nega, who was charged with supporting a terrorist group, Nega was found guilty in July 2012 and sentenced to 18 years in prison.

Read Freedom House reports 2013, Full report about Ethiopia


Source: http://www.freedomhouse.org/

Monday, November 18, 2013

Ethiopians demonstrate outside Saudi embassy in London

BBC - There's been growing anger among Ethiopians in and outside the country, about the way that some of their compatriots have been treated in Saudi Arabia.

Things came to a head following an ultimatum for illegal migrant workers to leave the country.

And there were clashes in Riyadh which led to several deaths last week.



On Monday, there have been demonstrations at Saudi embassies around the world. 

Friday, November 15, 2013

አዲስ አበባ ላይ በሳዑድ አረቢያ ኤምባሲ አጠገብ ሊካሄድ የነበረ የተቃዉሞ ሰልፍ በፖሊስ ተበተነ። ፖሊስ በመቶዎች የሚቆጠሩን ሰልፈኞች ለመበታተን ኃይል ተጠቅሟል!

የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳውዲ አረቢያ መንግሥት ጐን በመቆም ዋና ተባባሪ መሆኑን በዛሬው እለት አስመስክሯል



ሳውዲ ኤንባሲ ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ ሊያረጉ የነበሩት ያገሬ ልጆች በፈደራል ፖሊስ እደዚ ነበር የተበተኑት አስኪ ፈረዱ!


የሳውዲ መንግስትና ኢህአዴግ በተለያየ መንገድ ኢትዮጵያዊያንን ማጥቃት የቀጠሉ ቢሆንም በዛሬው እለት በየት/ቤቱ የታዩት ነገሮች ከሌላው ጊዜ በጣም የተለየ ነበር፡፡ ብዙ ተማሪዎች ጥቁር ልብስ በመልበስና በእረፍት ሰዓት ደግሞ ጧፍ በማብራት ሳውዲ በወገን ላይ እያደረሰ ያለው ስቃይና የመንግስትን ቸልተኝነት አውግዘዋል፡፡ከነዚህም ት/ቤቶች ውስጥ መድሀኒያለም ፣ባልቻ አባነፍሶ፣ኮልፌ እንዲሁም ሌሎች የመንግስትና የግል ት/ቤቶች በስፋት በዛሬው የጥቁር መልበስና የጧፍ ማብራት ስነ-ስርአት አድርገው ሀዘኛቸውን ገልጸዋል፡፡ሰኞና ከዛም በኋላ ባሉት ቀናት ተማሪዎቹ ከወገናቸው ጎን መቆም እንደሚቀጥሉ ይጠበቃል፡፡
--------------------------------------------------------------------
የኢትዮጵያ መንግሥት ከሳውዲ አረቢያ መንግሥት ጐን በመቆም ዋና ተባባሪ መሆኑን በዛሬው እለት አስመስክሯል!
በሳውዲ አረቢያ በሚገኙ ዜጎቻችን ላይ እየደረሰ ያለው በደል እና ስቃይ መጠኑ ከመጨመር አልፎ ሕይወትን እስከማሳጣት መድረሱ የሚታወቅ ነው፡፡ ይህን በደል እና ስቃይ ለመቃወም እና ሀዘናችንን ለመግለፅ በዛሬው ዕለት ማለትም ህድር 6 ቀን 2006 ዓ.ም አዲስ አበባ በሚገኘው በሳውዲ አረቢያ ኢምባሲ ፊት ለፊት ሰላማዊ ሰልፍ የተጠራ ቢሆንም በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ በአሰቃቂ እርምጃ ሰልፉ ሊካሄድ አልቻለም፡፡
እኛ ኢትዮጵያን በውጭ በሚገኙ ዜጐቻችን ላይ የሚደርሰው በደልና ግፍ እንዲቆም፣ ይህንንም ድርጊት የፈፀሙት ለሕግ እንዲቀርቡና የተጐዱ ዜጐች ተገቢውን ካሳ እንዲያገኙ፤ የኢትዮጵያ መንግሥትም በዜጐቹ ላይ ያሳየውን ቸልተኝነት በአስቸኳይ በማቆም ተገቢ የሆነውን የመንግሥት ኃላፊነት እንዲወጣ ቢጠየቅም፤ ሰልፉ በተቃራኒው በመንግሥት ታጣቂዎች በተወሰደ አሰቃቂ እርምጃ ተጠናቋል፡፡
በሳውዲ እየተፈፀመ ያለውን በደል በመቃወም በዓለም አቀፍ ደረጃ ኢትዮጵያዊያን ድምፃቸውን በማሰማት ላይ ቢሆኑም እኛ ኢትዮጵያዊያን ግን በገዛ ሀገራችን ድምፃችንን እንኳን እንዳናሰማ ታፍነናል፡፡ በዚህም እንቅስቃሴ ላይ የተሳተፉ የሰማያዊ ፓርቲ አመራሮች፣ አባላት፣ ደጋፊዎችና ሌሎች የኅብረተሰብ ክፍሎች ከፍተኛ ድብደባ፣ እንግልትና እስር ተፈፅሞባቸዋል፡፡
የመንግሥት ፖሊሶች የራሳቸውን ዜጋ በመደብደብና በማሰቃየት ብሎም በማሰር በሳውዲ በሚገኙ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ላይ የተፈፀመውን በደል ሀገር ውስጥ በሚገኙ ንፁሐን ወገኖቻቸው ላይ ደግመውታል፡፡
ይህ በውሸት ዲሞክራሲ ስም የተደበቀው አምባገነን መንግሥት ሕዝብን ለማሸማቀቅ የወሰደውን እርምጃ ወደ ጐን በመተው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቅድም አያቶቹን በማስታወስ ያስረከቡትን ክብር ከማስመለስ ወደ ኋላ እንደማይል እርግጠኛ መሆናችንን እንገልፃለን፡

Wednesday, November 6, 2013

BeraKing News(Ethiopia arrests 2 Journalists from independent paper.

<>   Ethiopia arrests 2 Journalists from independent paper
<> More than 75 publications have been forced to close under government pressure since 1993

Getachew Worku is being held without charge.
Ethiopian police have arrested without charge two editors of the leading independent Amharic weekly Ethio-Mihdar, according to local journalists.
Police in the town of Legetafo, north east of the capital Finfinne, (Addis Ababa), on Monday arrested Getachew Worku in connection a story published in October alleging corruption in the town administration, according to Muluken Tesfaw, a reporter with the paper, who spoke to Getachew shortly after his arrest. Getachew has not been charged, he said.
On Saturday, police arrested Million Degnew, the general manager of the newspaper, and Muna Ahmedin, a secretary, said Muluken and local journalists. Muna was released the same day but Million remains in custody without charge, Muluken said.
"A free and inquisitive media is a cornerstone of development that should benefit all Ethiopians," said CPJ's Africa Program Coordinator Sue Valentine. "Repeatedly detaining journalists without charge is an intimidation tactic that must end. We urge the authorities to release Million Degnew and Getachew Worku immediately."
The government has harassed Ethio-Mihdar in the past for its independent coverage, according to CPJ research. Million and Getachew have been sued for defamation by the public Hawassa University, according to local journalists and news reports. University officials are seeking 300,000 birr (US$15,000) and the closure of the newspaper over a report alleging corruption in the school's administration, according to local journalists.
In May, Muluken was detained for 10 days while reporting on evictions of Oromo & Gambela farmers from their land in north west Ethiopia. He was released without charge.
Ethiopia trails only Eritrea as Africa's worst jailer of journalists, according to CPJ's annual prison census. More than 75 publications have been forced to close under government pressure since 1993, CPJ research shows.

Ethiopia police 'torture and abuse' political prisoners

Ethiopia police 'torture and abuse' political prisoners

Protests earlier this year called for the release of political prisoners
Ethiopian authorities are torturing and mistreating political detainees to extract confessions, Human Rights Watch says.
The US-based group says former prisoners at the main detention centre in Addis Ababa described being beaten and kicked during interrogation.
It accuses Ethiopia of using anti-terrorism laws to stifle dissent.
The government has dismissed the report as biased and lacking credible evidence, according to AFP news agency.
The report by HRWsays police investigators at Maekelawi prison use illegal interrogation methods, keep inmates in poor detention conditions, and routinely deny them access to a lawyer.
Former detainees reported "being held in painful stress positions for hours upon end, hung from the wall by their wrists, often while being beaten", it said.
'Culture of impunity'
"Ethiopian authorities right in the heart of the capital regularly use abuse to gather information," said Leslie Lefkow, HRW's deputy Africa director.
"Beatings, torture, and coerced confessions are no way to deal with journalists or the political opposition."
Swedish journalist Martin Schibbye spent more than 400 days in an Ethiopian jail
She called on the Ethiopian government to "root out the underlying culture of impunity".
But Ethiopian authorities said the report was "extremely biased and ideologically marred".
"They haven't come up with any proof," government spokesman Shimeles Kemal told AFP. He criticised the study for basing its findings on testimonials from 35 former inmates and their families, rather than an on-sight investigation.
Among the former inmates interviewed was Martin Schibbye, a Swedish journalist convicted of entering the country illegally and supporting a rebel group.
Protesters took to the streets in the Ethiopian capital in June to demand the release of jailed journalists and activists.
It was the first major demonstration in Addis Ababa since 2005 when hundreds of protesters were killed in violence.
Ethiopia's Prime Minister Hailemariam Desalegn took office in September 2012 following the death of Meles Zenawi.
The Committee to Protect Journalists says the country is close to replacing Eritrea as the African country with the most journalists behind bars.http://m.bbc.co.uk/news/world-africa-24576942

Friday, November 1, 2013

ህወሓት አይድንም፤ እያቃሰተ ነው!!!



በጌታቸዉ አረጋዊ የህ.ወ.ሓ.ት ኣባልና የድምፅ ወያነ ጋዜጠኛ «ውራይና » የሚል በትግርኛ ቋንቋ የተዘጋጀ ለአራተኛ ጊዜ በነሃሴ ወር 2005 ዓ/ም የታተመ መፅሄት ስብሓት ነጋ የህ.ወ.ሓ.ት ፈላስፋ ቃለ መጠይቅ ያደረገበት መፅሄት በፅሞና ኣነበብኩት። የመፅሄቱ ዋና ይዘት ‹‹ህ.ወ.ሓ.ት እናድናት›› ነዉ የሚለዉ ስብሓት ነጋ በመፅሄቱ የተካተቱ ብዙ ስንክሳራዊ ሃተታ ተናግሯል ።
አሁን ማለት የፈለግኩት በመፅሄቱ የተካተቱ በሙሉ መልስ ለመስጠት አይደለም፡፡ ምክንያቱም የስብሓትን ስንክሳር መልስ ለመስጠት ከፈለኩ ግዜ አይገኝም መፅሃፍም ሊሆን የሚችል ነዉ። በመሆኑም አለፍ አለፍ በማለት የስብሓትን አንኳር አንኳር ነጥቦች መልስ ለመስጠት እሞክራለሁ።

ሌላ ይህ ፅሁፍ መልስ ለመስጠት የተገደድኩት የ ህ.ወ.ሓ.ት መሪዎች ለትግርኛ ቋንቋ ማዳበርን በትግርኛ ስነ-ፅሁፍ ለማስፋት ብለዉ በፅሁፍ ቢናገሩ እጅጉን የሚደገፍና የትግራይ ህዝብ መስዋእት ነበር። ይህ ደግሞ ማንም ኢትዮጵያዊ ይድግፈዋል፤፤

የ ህ.ወ.ሓ.ት መሪዎች ግን ከረጅም ጊዜ ጀምረዉ ለትግራይ ህዝብ በጠባብነት ለመነሳሳት ሲፈልጉ ወይ መምቻ ሃይል ሊጠቀሙበት ሲፈልጉ የሚናገሩት የሚፅፉበት ኢትዮጵያዊ አጀንዳ እያለና ያለ ትግራይ ህዝብ የሚነገር የሁሉም ኢትዮጵያዊ ጉዳይ አድርገዉ እንደመናገር ፈንታ በድብቅ ይናገራሉ።

ስብሓት ነጋም በአሁኑ ጊዜ በኢትዮጵያ ሃገራችን ብዙ ደንቃራ ሁኔታዎች ተደቅነውባትና ህዝቡ በብዙ ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ፖለቲካዊ ችግሮች አጋጥመውት እያሉ ለትግራይ ለአንድ ክልል ከ4-5 ሚሊዮን ህዝብ ያላት ለብቻዋ የሚወከል ህ.ወ.ሓ.ት ትንሳኤ መተንበይ ሌላዉ የኢትዮጵያ ህዝብና ክልሎች … በሂወት ካሉት በታች ከሞቱት በላይ የሆኑ ህዝቦችና ክልሎች እንደማሰብ ትግራይን ጨምሮ ማለት ነዉ። ለትግራይ ብቻ ማሰብ ለስብሓት ነጋ ጠባብ ሊያስብላቸዉ የሚችል ይመስለኛል።

በሌላ በኩል የስብሓት ነጋ ትንሳኤ ሙዉታን ሲለን የህ.ወ.ሃ.ት ትንሳኤ ሙታን ለመመለስና የህ.ወ.ሃ.ት መሪዎች ከመሰነጣጠቅና ከመክሰም እንዴት እናድነዉ ጭንቀቱ እንጂ የትግራይ ህዝብ ባጠቃላይ የሃገራችን ህዝቦች ብሄር ብሄረሰቦች ከዲሞክራሲና ሰብኣዊ መብቶች ነፃነትና አፈና አስተዳደር እንዴት እናድናት አይደለም ጭንቀቱ፤፤ ይህ ካልኩ በኃላ ወደ መፅሄቱ ላይ የሰፈረዉ አንዳንድ መልስ ለማስቀመጥ እሞክራለሁ።

ስብሓት ነጋ በአሁኑ ጊዜ ያለዉ የህ.ወ.ሓ.ት አመራር ለነዚህ ለአመታት እያጠራቀማቸዉ የቆየ ችግርን በፍፁም ነፃነት በፍፁም አባታዊነት በትክክል ከተረዳቸዉ መረዳትም ያለበት ነዉ።‹‹የ ህ.ወ.ሓ.ት ትንሳኤ ጊዜ ይወስዳል እንጂ ድላችን የማይቀር ነዉ።›› ይላል ውራይና መፅሄት ነሃሴ 2005 ገፅ 4 ሶስተኛ አምድ አዲስ መስመር ሁለት

ስብሃት ነጋ ከእንግዲህ ወዲህ የምናውቀዉ ህ.ወ.ሓ.ት ከነበሩበት ብዙ ችግሮች ሲያሳየዉ የነበረ መገላበጥ የተሳሳቱ ሃገራዊና አህጉራዊ አቋሞች በተለይ ደግሞ በሃገር ሉኣላዊነት የሚመለከት ሃገራዊ ሃላፊነት የጎደለዉ ብዙ ስህተትና ጥቁር ነጥብ ቢሰራ በፀረ-ደርግ የነበረዉ አቋም የኃላ ኃላ ለስልጣኑና የግዛቱን ማስፋፋት ሲል ያመጣዉ አገር አቀፍ አመለካከት ለኢትዮጵያ ህዝብ ለጊዜዉ ከፋሽስታዊ ደርግ አፈና አድኖታል። ተነፃፃሪ ሰላም ያመጣ ይመሰል ነበር ሆኖም ግን የህ.ወ.ሓ.ት አመራርና እሱን እሚመስሉ እሱ የፈጠራቸዉ የህ.ዋ.ሓ.ት ስሪት ፓርቲዎች ልክ ደርግ መጀመሪያ ወደ ስልጣን ሲመጣ ኢትዮጵያ ትቅደም ያለ ምንም ደም እንዳለና ቀስ በቀስ ወታደራዊ ባህሪዉ አገርሽቶበት ፍፁም ለኢትዮጵያ ህዝብ ፋሽስትና ፀረ ህዝብ የሆነዉ የህ.ዋ ሕ.ት መሪዎች የትግራይ ህዝብና ልጆቹ በሃገር ደረጃ ደርግ ከተደመሰሰ ብቻ ነዉ ሰላም፣ ፍትህ፣ ዲሞክራሲ፣ ነፃነት፣ የህግ የበላይነት ይመጣል እያለ በመቶ ሺዎች ዜጎች የሰጡትን ደርግን አስወግዶ ወንበሩን ከተቆናጠጠ በኃላ ትላንትና ሽሮ አለ መረቅ አለ እያለ ወደ እሳት እየማገደዉ የመጣ ለመጀመሪያ ጊዜ የተከዳ የትግራይ ህዝብ ነበር። ውጤቱ ደግሞ የትግራይ ህዝብ ሳይሆን መላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ በአሁኑ ጊዜ አግኝቶት ያለ ምንድነዉ ?

Saturday, October 26, 2013

የህዋሃት ጀነራል መኮንኖች በሃብት ብዛት እየተመፃደቁ ነው!!!


                                             ጄ/ል ሞላ ሃ/ማሪያም
የጀነራል መኮንኖች የምደባ ለውጥ ተካሄደ !
ሜጀር ጀነራል አደም መሀመድ የአየር ሀይል አዛዥ ሆነው መሾማቸውንና የአዛዥ ጄነራሎች ላይም የምደባ ለውጥ መደረጉን ፡፡ በአየር ሀይል አዛዥ በነበሩት ሜጀር ጀነራል ሞላ ሀይለማርያም ምትክ የተሾሙት ሜጀር ጀነራል አደም መሀመድ  አቢዬ ግዛት የሠላም አስከባሪ ሀይል ምክትል አዛዥነት ያገለገሉ እንዲሁም የመከላከያ ዘመቻ መምሪያ ኃላፊ ነበሩ፡፡
በሌሎች የመከላከያ የስራ ምድብ ቦታዎች ላይ የአዛዦች የምደባ ለውጥ መደረጉን የተናገሩት ምንጮች፣ አዲስ የሀላፊነት ምደባ ከተሠጣቸው ውስጥ ሌተናል ጀነራል ሠአረ መኮንን፣ ሌተናል ጀነራል አበባው፣ ሜጀር ጀነራል ዮሀንስ ወልደጊዮርጊስ፣ ሜጀር ጀነራል ገብራት አየለ እና ሌሎችም ይገኙበታል፡፡
የህዋሃት ጀነራል መኮንኖች በሃብት ብዛት እየተመፃደቁ ነው!
Ethiopian generals, who for the vast majority are Tigrayan, have a good many material advantages, such as free petrol (gasoline), an official car, free electricity and water, to name but a few. However, in some cases, these advantages can go even further, such as the possibility to import domestic equipment financed by the ministry for defence. They have also benefited from plots of land in the Bole neighbourhood in Addis Ababa and some of these generals were attributed official housing during the time when the late Meles Zenawi was Prime Minister. Some of them, like General Tadesse Gawna and Colonel Tsehaye Manjus, had no qualms about selling the plots of land they had been attributed. Others rent their official dwellings to third parties. One who does precisely this is General Gezae Abera who headed the army logistics department before going to live (asylum) in Sweden. Others are Generals Gebre Egziabher Mebratu, Teklai Ashebir and Fisseha Kidane, who receive monthly rents of between 30 and 40,000 birrs (€1100 to €1500) each.

Monday, October 21, 2013

Call for a Peaceful Rally in Bergen, Norway!



A statement from the Organizing Committee of the peaceful rally.

We, members of the Oromo community residing in Bergen, Norway, neighboring communities and friends of Oromo, are very concerned about human rights violations particularly against the Oromo in Ethiopia. Therefore, we have a plan to have a peaceful rally against the dictatorial regime in Ethiopia on October 25, 2013.

Time and Place:
The demonstration will be held on the 25th October 2013 from 13.00 to 15.00. We will gather at the Blue Stone, and we will head through the gallery, pass along the exhibition center and move all the way to the police station and, there, deliver a letter to the person in charge.

Aims:


• We shall demonstrate against human rights violations by the dictatorial regime in Ethiopia. We will turn to the new Norwegian government to press the Ethiopian government to respect human rights and release all political prisoners.

• Call for the release of Bekele Gerba, Mesfin Abebe and other political prisoners in Ethiopia.

• Candlelight vigil to remember the Oromo activist Engineer Tesfahun Chamada, who died in the Kaliti Prison after a horrible and inhuman torture by the Ethiopian government. And victims of the Kofalee Massacre of August 2013.

All protesters are welcome to join us to stand against, and say ‘no’ to the dictatorial and tyranny government.

Regards,

Dandana Bafkane,
Dejene Sorry,
Members of the Committee

For Further information, contact: Abdi Gameda Chali (Tel. +4794724502)

የወያኔ ቀጣይ የፖለቲካ ሴራዎች?

የወያኔ ቀጣይ የፖለቲካ ሴራዎች

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

እንደ መንደርደሪያ
የሁለት ሺህ ስድስት ዓመተ-ምህረት የመጀመሪያ ወር ተጠናቅቋል፤ አዳዲስ ክስተቶችም ታይተዋል፤ ያለፉት አስራ ሁለት
ዓመታትንበጃንሆይ ቤተ-መንግስት ያሳለፉት ፕሬዝዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ፣ በኦህዴዱ ሙላቱ ተሾመ መተካታቸው አንዱ
ነው፡፡ አባይ ፀሀዬና ዶ/ር ካሱ ኢላላም ከበረከት ስምዖንና ኩማ ደመቅሳ በተጨማሪ በሚኒስትር ማዕረግ የኃ/ማሪያም ደሳለኝ
‹‹የፖሊሲና ጥናት ምርምር›› አማካሪ ሆነው መሾማቸው ሌላው ነው (በነገራችን ላይ ሹመቱን እንደተለመደው አይቶ ችላ ብሎ
ለማለፍ የማያስችሉ ሶስት ምክንያቶች አሉ፤ የመጀመሪያው በሀገሪቱ ለአንድ የሥራ መደብ አራት ሚንስትር ተሹሞ አለማወቁ
ሲሆን፤ ሌላው ተሿሚዎቹ፣ ኢህአዴግን ከመሰረቱት አራት ፓርቲዎች በኮታ የተወጣጡ መሆናቸው ነው፡፡ ሳልሳዊውና
አስገራሚው ደግሞ ሰዎቹ ፖለቲከኞች እንጂ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ ጥናትና ምርምር ያካሄዱ ምሁራን አለመሆናቸው ነው)
እነዚህ ሁሉ በግልፅ የሚታወቁ የዓመቱ መጀመሪያ ክስተቶች ናቸው፡፡ ለስርዓቱ ቅርበት ካላቸው ምንጮቼ ባገኘሁት መረጃ
መሠረት፣ በቅርቡ ‹ሚዲያ›ን እና ‹የይቅርታ ስነስርዓት›ን የተመለከቱ አዳዲስ አዋጆች በተወካዮች ም/ቤት ለመፅደቅ
ተዘጋጅተዋል፡፡ በተለይም ‹ሚዲያው›ን የሚመለከተው አዲሱ ህግ፣ ከአምስት ዓመት በፊት ተግባር ላይ የዋለውን የ‹‹ፕሬስ
አዋጁ››ን የአፋና ጉልበት ይበልጥ የሚያጠናክር በመሆኑ፣ የነበረው አንፃራዊ ጭላንጭል ጭራሽ ሊዳፈን እንደሚችል መረጃዎች
ያሳያሉ፡፡ ‹‹የይቅርታ አዋጁ››ም ቢሆን ጥቂት የአገዛዙ ጉምቱ ባለስልጣናት ‹‹የተቃዋሚ ፓርቲ የአመራር አባላትና አንዳንድ
የግል ጋዜጠኞች ብንታሰርም በይቅርታ እንፈታለን በሚል ግንባሩን እየተፈታተኑ ነው›› ሲሉ ደጋግመው መደመጣቸውን፣
ከአዲሱ ‹‹የይቅርታ አሰጣጥ እና አፈፃፀም ሥነ-ሥርአት አዋጅ›› ጋር ካያያዝነው፣ አንቀፆቹ ሊኖራቸው የሚችለውን አንድምታ
መገመቱ ብዙ ከባድ አይሆንም፡፡
ለማንኛውም ኢህአዴግ ከመቼውም ጊዜ በላይ ጉልበታም በመሆን ቀጣዩን ምርጫ በስኬት ለማለፍ፣ በያዝነው ዓመት የተለያዩ
አፋኝ ህጎችን በማውጣት ፓርቲዎቹን የማዳከም ስራ ለመስራት በተለየ መልኩ መዘጋጀቱ ተሰምቷል፡፡ በአናቱም ኃ/ማርያም
ደሳለኝ-ከመንግስት፣ ከፓርቲውና ከውስን የግል ጋዜጠኞች፤ ደመቀ መኮንን-ከአዲስ ዘመን ጋዜጣ፤ ሽመልስ ከማል -ከኢዜአ ጋር
ያደረጓቸው ቃለ-መጠይቆችም ይህንን መረጃ የሚያጠናክር ሆኖ አግኝቸዋለሁ፡፡ የዚህ ፅሁፍ ተጠየቅም አገዛዙ በቀጣይ ሊኖረው
የሚችለውን ባህሪ እና ‹አምስተኛው ዙር ሀገር አቀፍ ምርጫ›ን አስቀድሞ ለማሸነፍ እየቀመረ ያለውን ሴራ መጠቆም ነው፡፡

Friday, October 18, 2013

Political prisoners tortured in Ethiopia



Political prisoners tortured in Ethiopia



Addis Ababa : Political prisoners in Ethiopia held under inhumane conditions and tortured regularly, says Human Rights Watch

In a report that Human Rights Watch publishes, based on 35 interviews, says former prisoners Maekelawi prison in the capital Addis Ababa that they were beaten, kicked and beaten with sticks and rifle butts during interrogation.

Others say that they were hung by the wrist in painful positions for hours while they were beaten.




Ethiopian authorities rejected the report as a lie. Government spokesman Shimeles Kemal says it is one-sided, ideologically colored and that the missing evidence.




According to HRW, most sitting in the previously unknown Maekelawi prison political prisoners, who are to receive visits by lawyers or relatives.

HRW accused the Ethiopian authorities to use anti-terror laws to remain silent in death political opponents and journalists.

Tuesday, October 15, 2013

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰልፍ ክልከላ ቀጭን መስመር

የጠቅላይ ሚኒስትሩ የሰልፍ ክልከላ ቀጭን መስመር?



ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ መስከረም 24 ቀን 2006 ዓ.ም. ከጋዜጠኞች ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች ለሁለተኛ ጊዜ ማብራሪያ ሰጥተዋል፡፡


በበርካታ ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ገለጻ ያደረጉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች ሰልፍ የማድረግ ሕገ መንግሥታዊ መብት ዙሪያ የሰጡት ምላሽ ግን አነጋጋሪ ሆኗል፡፡

የአዲስ አድማስ ጋዜጠኛ ኤልሳቤጥ እቁባይ ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ያቀረበችው ጥያቄ የሚከተለው ነበር፡- ‹‹የትግል እንቅስቃሴአቸውን አገር ውስጥ እያደረጉ ያሉ የፖለቲካ ፓርቲዎች በተለያዩ ጊዜዎች በተለያዩ ከተማዎች ከመንግሥት ምላሽ ይፈልጋሉ ባሏቸው ጉዳዮች ላይ ሰላማዊ ሰልፎችን አድርገዋል፡፡ ምንም እንኳን ሰልፎቹን አስመልክቶ በመንግሥት ኮሚኒኬሽን በኩል የተሰጡ መግለጫዎች ቢኖሩም ሰላማዊ ሰልፉ ላይ ከቀረቡ ጥያቄዎች ‹ምላሽ ያሻቸዋል፣ አግባብነት አላቸው› ብለው መንግስትም በተለያየ መንገድ ከሚሰበስባቸው መረጃዎች የወሰዷቸው ጥያቄዎች አሉ ወይ››

ለጥያቄው በጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሰጠው ምላሽ ለብዙዎች የሚያረካ ነበር ለማለት ያስቸግራል፡፡ ይልቁንም ምላሹ ሌሎች ተጨማሪ በርካታ ጥያቄዎችን አስነስቷል፡፡ በመልሳቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ ሕገ መንግሥታዊ መብት መሆኑን፣ መንግሥታቸው በጫና ሐሳቡን የሚቀይር እንዳልሆነ፣ ተመሳሳይ ጥያቄዎች በተደጋጋሚ ከተጠየቁ መንግሥት አንድ ቦታ ላይ እንደሚያቆመው፣ የፓርቲዎች መብዛት ሰልፉን እንዳበዛው፣ ሰልፉ የሚታወቀው ውጭ ባሉ የእቅዱ ባለቤቶች እንደሆነ ገልፀዋል፡፡

Saturday, October 5, 2013

ቀጣዩ የኢሕአዴግ ዒላማ ማኅበረ ቅዱሳን ይኾን?

ቀጣዩ የኢሕአዴግ ዒላማ ማኅበረ ቅዱሳን ይኾን?


(ፋክት መጽሔት፤ ቁጥር 14 መስከረም ፳፻፮ ዓ.ም.)






ተመስገን ደሳለኝ

የኢሕአዴግ ታጋዮች የመንግሥት ‹‹ጠንካራ ይዞታ›› የሚባሉ ከተሞችን ሳይቀር መቆጣጠር ችለዋል፤ ወደ አዲስ አበባም የሚያደርጉት ግሥጋሴም ፕሬዝዳንት መንግሥቱ ኃይለ ማርያምን ሳይቀር ዕንቅልፍ ነስቷል፡፡ በአንዳች ተኣምር ግሥጋሴውን መግታት ካልቻሉ በጥቂት ወራት ውስጥ ሁሉም ነገር ታሪክ እንደሚኾን በማወቃቸው መላ በማፈላለጉ ላይ ተጠምደዋል፡፡ በዚህን ጊዜ ነበር(የሐሳቡ አመንጪ ተለይቶ ባይታወቅም)፣ ‹‹ለዩኒቨርስቲ ተማሪዎች አጭር ሥልጠና ሰጥቶ ከሀገሪቱ ሠራዊት ጎን ማሰለፍና የ‹ወንበዴውን ጦር› ማድረሻ ማሳጣት›› የሚለው ሐሳብ እንደ መፍትሔ የተወሰደው፡፡

እናም መንግሥቱ ራሳቸው ተማሪዎቹን በዩኒቨርስቲ አዳራሽ ሰብስበው እንዲህ ሲሉ አፋጠጧቸው፡- ‹‹እነርሱ (ኢሕአዴግና ሻዕቢያን ማለታቸው ነው) ለእኵይ ዓላማቸው ከእረኛ እስከ ምሁር ሲያሰልፉ እናንተ ምንድን ነው የምትሠሩት? በሰላማዊ ሰልፍና በስብሰባ ብቻ መቃወም ወይስ ወንበዴዎቹ እንዳደረጉት ከአብዮታዊ ሠራዊታችነ ጎን ቆማችኹ የአገሪቱን ህልውና ታስከብራላችኹ?››

ይህን ጊዜም አስቀድሞ በተሰጣቸው መመሪያ ከተማሪው ጋራ ተመሳስለው በአዳራሹ የተገኙት የደኅንነት ሠራተኞችና የኢሠፓ ካድሬዎች ‹‹ዘምተን ከጠላት ጋራ መፋለም እንፈልጋለን›› ብለው በስሜትና በወኔ እየተናገሩ በሠሩት ‹ድራማ› ተማሪው ትምህርት አቋርጦ እንዲዘምት ተወሰነ፤ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲም ተዘጋ፤ ተማሪዎቹም ለወታደራዊ ሥልጠና ደቡብ ኢትዮጵያ ወደሚገኘው ብላቴ የአየር ወለድ ማሠልጠኛ ከተቱ፡፡

ከመላው ዘማቾች ዐሥራ ሁለት የሚኾኑ ተማሪዎች ተሰባስበው ሲያበቁ በየቀኑ ካምፓቸው አቅራቢያ ወደሚገኘው ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በመሄድ ከመዐቱ ይታደጋቸው ዘንድ ፈጣሪያቸውን በጸሎት መማጠን የሕይወታቸው አካል አደረጉት፤ ከቀናት በኋላም በአንዱ ዕለት አንድም ለመታሰቢያና ለበረከት. ሁለትም ስብስቡ ሳይበተን ወደፊት እንዲቀጥል በሚል ዕሳቤ ‹‹ማኅበረ ሚካኤል›› ብለው የሠየሙትን የጽዋ ማኅበር መሠረቱ፡፡ . . . ይኹንና ከመካከላቸው አንዳቸውም እንኳ በ፲፱፻፸፯ ዓ.ም በፓዌ መተከል ዞን የተደረገውን የመልሶ ማቋቋም ሠፈራ ፕሮግራም እንዲያመቻቹ በዘመቱ ተማሪዎች ከተመሠረተውና ከተለያዩ የጽዋ ማኅበራት ጋራ በመዋሐድ የዛሬውን ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን›› እንደሚፈጥሩ መገመት የሚችሉበት የነቢይነት ጸጋ አልነበራቸውም፤ የኾነው ግን እንዲያ ነበር፡፡



ማኅበረ ቅዱሳን

የ‹‹ማኅበረ ሚካኤል›› መሥራቾች ከተማሪ ጓደኞቻቸው ጋራ ‹‹ይለያል ዘንድሮ የወንበዴ ኑሮ››ን እየዘመሩ የገቡበት ወታደራዊ ሥልጠና ተጠናቅቆ ወደ ጦር ሜዳ ከመግባታቸው በፊት ዐማፅያኑ አሸንፈው የመንግሥት ለውጥ በመደረጉ ሥልጠናቸውን ሳይጨርሱ ወደየመጡበት ተመለሱ፡፡ ኾኖም ለውጡ በተካሄደ በዓመቱ እነርሱን ጨምሮ በአምላካቸው፣ በጻድቃን፣ በሰማዕታትና በመላእክታት ስም የተመሠረቱ[ከአቡነ ጎርጎርዮስ ዘንድ ሲማሩ የቆዩ] የተለያዩ ማኅበራት ተሰባስበው ወደ አንድ እንዲመጡ መደረጉ ሊጠቀስ የሚገባ ልዩነት ባይፈጥርም ስያሜው ግን ብርቱ ክርክር አሥነሳ፤ አቡነ ገብርኤልም ‹‹ማኅበረ ቅዱሳን ብዬዋለኹ›› ብለው ውጥረቱን አረገቡት፡፡ ዕለቱም[ልደቱን የሚቆጥርበት] ግንቦት ፪ ቀን ፲፱፻፹፬ ዓ.ም. እንደነበር ተጽፏል፡፡

ዓላማው ምንድን ነው?

Sunday, September 29, 2013

[Breaking News] Andinet/UDJ party demonstration kicks off in Addis | September 29, 2013

ጫካው ሕግ ከተማ ውስጥ አይሰራም!!
መንግስት ነኝ ባዩ የዱርዬ ስብስብ የጻፈውን ሕገ መንግስት ያክብር

 ካላወቀው ሕግ የሚተርጉም አስተርጓሚ ይመድብ 22 ዓመት የጻፈውን ሕግ የማያውቅ ሰልጣኑን ባስቸኳይ ይልቀቅ!

Sunday, September 15, 2013

Peaceful Demonstration, Candle Light Vigil for Engineer Tesfahun Chemada and Kofale massacre by Oromo Youth Association in Norway




On September 14, 2013 Oromo Youth in Norway protested against human rights violations and brutal killing by the dictator Ethiopian government. The main objective of the demonstration was to condemn the human right violation in Ethiopia and the ethnic based abuses as a result of which many Oromos are being arrested, tortured, killed, and thousands are disappearing. The trend of repression is increasing alarmingly and huge number of Oromos have been jailed, tortured and exposed to inhuman conditions under fabricated charges. The TPLF/EPRDF leadership has a standing policy of protracted attack against the Oromo people irrespective of age, sex, profession and occupation. To criminalize Oromo, being only Oromo is enough in Ethiopia.
Among the recent victims is Engineer Tesfahun Chemeda who died in kaliti prison, the massacred Muslim Oromos in Kofale and the genocide against Oromos in Anniyyaa, Oromia.
According to Amnesty International, the Ethiopian regime stifled freedom of expression, severely restricting the activities of the independent media, political opposition parties and human rights organizations. Dissent was not tolerated in any sphere. The authorities imprisoned actual and perceived opponents of the government. Peaceful protests were suppressed. Arbitrary arrests and detention were common, and torture and other ill-treatment in detention centers were rife. Forced evictions were reported on a vast scale around the country.

Among the recent victims is Engineer Tesfahun Chemeda who died in kaliti prison, the massacred Muslim Oromos in Kofale and the genocide against Oromos in Anniyyaa, Oromia.
According to Amnesty International, the Ethiopian regime stifled freedom of expression, severely restricting the activities of the independent media, political opposition parties and human rights organizations. Dissent was not tolerated in any sphere. The authorities imprisoned actual and perceived opponents of the government. Peaceful protests were suppressed. Arbitrary arrests and detention were common, and torture and other ill-treatment in detention centers were rife. Forced evictions were reported on a vast scale around the country.

Saturday, September 14, 2013

Statement of peaceful demonstration of the Oromo Community in the United Kingdom




Today, 13 September 2013, members of the Oromo Community in the UK, protested against human rights violations and brutal killing exercised by the criminal Ethiopian Government.
The aim of the protest was to stand against Human rights abuses and the brutal killings of thousand s of Oromos including Engineer Tesfahun Chemeda and the Massacred Muslim Oromos in Arsi. The arbitrary arrest, torture, extra-judicial killings, mass murder & disappearances are not only the day- to- day practices in Ethiopia, but also reached the highest peak. For example, the Oromia Support Group in United Kingdom, a non-political organization that raise awareness of human rights violations in Ethiopia, has reported four thousand two hundred seventy nine (4,279) extra-judicial killings and 987 disappearances of civilians in Ethiopia from 1994 – 2010. These figures do not include the unreported killings and secret arrests that are exercised at several corners in the country particularly in Oromia region. The recent shocking incidents were the killings of twenty- seven innocent civilians including five children in Kofale, Arsi region of Oromia on August 3, 2013. http://www.amnesty.org/en/news/ethiopian-repression-muslim-protests-must-stop-2013-08-08 and the murder of Engineer Tesfahun Chemeda who has been tortured and killed in Kaliti prison custody on August 24, 2013.

The surprising news was that, despite all the repressions and killings, the Ethiopia Government was privileged to be the top aid recipient in Africa. Currently, the Ethiopian government is receiving $500,000,000 every year ($2 billion in the next 4 years) from the UK government alone.http://www.voanews.com/content/ethiopia-is-top-uk-aid-recipient-117204413/157544.html.. According to the current trend, the size of this aid is increasing and there is also a plan for huge investment at the cost of poor Oromo farmers’ displacement due to the land grab. The donors say ‘’we are trying to help the millions of very poor, very vulnerable Ethiopians improve their lives’’. But the reality on the ground is that they are financing the government who is terrorizing and suppressing its people and increasing poverty, while enriching the government officials and few of their cliques.
A number of independent bodies accused the Ethiopian government for using the aid money for repression and sidelining the opposition into submission. Also the Ethiopian Government officials openly use their power to enrich their families and close friends with the aid money. The corruption, poverty and injustice increased alarmingly at a higher rate in Ethiopia as the aid money goes up. Sowhere is the help for the poor?
We believe that the UK and US Governments are fully aware of all sorts of human rights abuses exercised by the Ethiopia Government.
http://allafrica.com/stories/201304231206.html?viewall=1. However, they give deaf ears to these repressive and brutal government actions and provide the huge tax payers’ money and give moral and technical supports. Therefore, we appeal to the UK government, the US government and the international community:
To stop indirect or direct involvements in activities suppressing the struggle of the Oromo and other victims of the brutal Ethiopian Government by revising their aid plan.
To seek justice for Engineer Tesfahun Chemeda who has been murdered while he was under the custody of the Ethiopian regime.
To seek justice for the twenty seven innocent Muslims, including 5 children, who have been massacred in Kofale, Arsi region of Oromia by the Ethiopian Government?
To support the Oromo and other victimized communities in Ethiopia to overcome injustice and help them to live in freedom, peace, and democracy and achieve stability in the region.
The Oromo community in the UK

Sunday, September 8, 2013

Demonstration in Norway on September 14, 2013

Oromo Struggle For Freedom







The Oromo Youth Movement in Norway, together with Oromo nationalists has finished its preparation to hold demonstration on Saturday September 14, 2013



Place: From Oslo Central Station to Parliament

Time: 13:00-16:00



The Object of the demonstration,



Condemning the cold blooded massacre of our people by TPLF/EPRDF federal police in Kofale town, Arsi Zone of Oromia Region.

Call for a Reversal of Racial and Politically Motivated Sentences of the Oromo university students by the TPLF/ EPRDF.

Condemning the escalating human rights violation, Land grabbing and the ethnic cleansing of the Oromos by Leyu Police of the EPDRF in Harage



Mourning candle Program for the death of the Oromo activist Engineer Tesfahun Chamada in Kaliti Prison in a horrible & inhuman torturing by the Ethiopian government.

Sunday, September 1, 2013

Breaking News Interview With semayawi party chair person Eng yilkal getnet

የወያኔ ፌደራል ፕሊሶች ሰማያዊ ፓርቲ ቢሮ በመሰበር ንብረታቸውን ዘርፈዋል :: በአባላቶቹ ላይ ክፉኛ ድብደባ ደርሶባቸዋል :: ሴቶች አበላቶችን ጭቃ ላይ በማሰበርከክ እና ክፉኛ በመደብደብ አካላቸው ላይ ክፉኛ አደጋ አድርሰዋል ::


የፓርቲው ሊቀመንበር ኢንጅነር የልቃል ገዳም ሰፈር ፕሊሰ ጣቢያ በመውሰድ ሰድብና ዘለፋ አድርሰውባቸዋል :: የፓርቲው ቢሮ በፌደራል ፕሊሰ ተከብዋል ማንም መግባት አይቻልም ..ለሰልፍ የተዘጋጁት ቂሳቂሶች በሙሉ በፌደራል ፕሊሰ ተዘርፈዋል:: በርካት ያሉ አባሎችም የደረሱበት አልታወቀም :

Monday, August 26, 2013

አሳዛኝ ዜና !ኢንጂነር ተስፋሁን ጨመዳ ወኅኒ ውስጥ አረፉ



የሽብር ክሥ ተመሥርቶባቸው የዕድሜ ልክ እሥራት የተፈረደባቸው ኢንጂነር ተስፋሁን ጨመዳ ለሰባት ዓመታት እሥር ላይ ከቆዩ በኋላ እዚያው ወኅኒ ውስጥ ማረፋቸውን ቤተሰቦቻቸው ለቪኦኤ ገለፀዋል፡፡


ፖሊስ የሰጠውን ማስረጃ አይተናል ያሉት እስከፍርዱ ድረስ ከይግባኝ በፊት ቆመውላቸው የነበሩት ጠበቃ አቶ ጥላሁን ታደሰ ኢንጂነር ተስፋሁን ያረፉት ባለፈው ዓርብ ሌሊት መሆኑን አመልክተው የፖሊሱ መረጀ እራሣቸውን ማጥፋታቸውን እንደሚጠቁም ጠቁመዋል፡፡


ኢንጂነር ተስፋሁን እራሣቸውን አጥፍተዋል የሚለውን መግለጫ ለማመን እንደሚቸገሩ የሚናገሩት አቶ ጥላሁን ታደሰ ሕክምና እንዲደረግላቸው በተደጋጋሚ ሲጠይቁ እንደነበረና የጠየቁትን አለማግኘታቸውን እንደሚያውቁ፤ ከእህታቸው ጋርም በማግስቱ ለመገናኘት ቀጠሮ ይዘው እንደነበረ ቤተሰብ እንደነገራቸው ገልፀዋል፡፡


Friday, August 23, 2013

መታየት የሚገባው......እውነትም ኢትዮጵያ ብዙ መልካም ሰዎች አሏት ...ትልቅ ተስፋ ነው!

መታየት የሚገባው......እውነትም ኢትዮጵያ ብዙ መልካም ሰዎች አሏት ...ትልቅ ተስፋ ነው!
The Justice System Becoming a Political Tool in Ethiopia

Calls for Reversal of Racially and Politically Motivated Sentences

The Federal High Court of Ethiopia sentenced 21 Oromo Nationals (most of whom are university students) to as much as 2-8 years in prison on 7th August, 2013. The report HRLHA received indicates that all of them have spent about three years pending trials on alleged charges of collaborating with the opposition organization of Oromo Liberation Front with the intention of committing terrorist crimes. According to information obtained by HRLHA through its correspondents, most of the defendants were very young Oromo students picked up at different times from different universities and colleges in the regional state of Oromia and other parts of the country.

The HRLHA has learnt that most of the 21 Oromo defendants did not even have acquaintance of each other, let alone collectively committing terrorist crimes, as they were brought together from different universities in the country and met each other in the jail. According to some legal experts, the fact that the charges were mere fabrications aimed at imposing punishments intended for political intimidations has made it difficult for the accused to defend themselves. However, by blatantly acting as a political tool of the ruling party, the court handed down the guilty verdict on the Oromo nationals without taking into consideration some evidences that the defendants attempted to present to defend themselves against the charges. There are more concerns that particularly five of the twenty one defendants who were charged with additional and separate article (criminal code, article 241,“Attack on the Political or Territorial Integrity of the State”, from the sixteen others might face very harsh punishments.

Although this sentence did not come as asurprise, as it is not the first of its kind, it has enormously added to the accumulation of partiality, injustice and unfairness of the justice system, raising further concerns among the human rights groups, and defenders of justice and equality including the HRLHA.

The twenty one alleged convicts are

No Name Year of sentence University Sex

1Dachassa Wirtu Mosisa Haromaya M

2 Ebissa Ratessa Ambo 8M

3Getu Saketa Finfine (Addis Ababa)M

4Diribsa Damte Jote 8 Finfine(Addis Ababa)M

5Adamu Shiferra 8Finfine (Addis Ababa)M

6Sena Merera 3 Arba Minch M

7Silashi Sori 3 Haromaya M

8Abdisa Gudeta 3 14 Mada Walabu M

9Miressa HYesus 3 Finfine (College student)M

10Abdi Dereje 4 Wallega M

11Deme Zerhun 4 Finfine (College Student) M

12Alemayehu Regassa 3 Hawasa M

13 Shafi Said 3 Jimma M

14 Dagim Bekele 3 Adama M

13 Lami Jirata 4 Teacher (Finfine) M

14 Birhanu Imiru 4 Teacher(Kotobe Coolege) M

15 Alemu Teshome Jirata 3 Journalist (Finfine) M

16 Shashe Said 3_F

17 Getachew Abera 3 Wallaga (Shambu)M

18 Dereje Getu 3-M

19 Jirenya Dessaleg n3_M

20 Lemi Wegga 4 Teacher M

21Alemu Teshome 3_M

Dachassa Wirtu Diribsa Damte Sena Merera

The Human Rights League of the Horn of Africa calls up on the Ethiopian Government to reverse this unfair verdict and unconditionally release the prisoners. It also calls up on all local, regional, and international activists of justice and human rights defenders to jointly raise their voices against such racial partialities and injustices so that the Ethiopian Government refrain from inappropriately using the justice system as a weapon of punishment and intimidation for political gains

Ogaden and Oromo Refugees At Severe Risk

Ogaden and Oromo Refugees At Severe Risk

The Oromia Support Group (OSG), a non-political organisation, in association with the Oromo Relief Association UK, have released a report which compiles information obtained from Oromo and Ogaden refugees in South Africa in October and November 2012. The report intends to raise awareness of human rights violations in Ethiopia.
Fifty-eight Oromo and two Ogadeni refugees from Ethiopia were interviewed in Johannesburg, Alexandra township and Randfontein, in Guateng province, and in Kinross and Evander, Mpumalanga province, in October and November 2012.The refugees reported serious abuse in Ethiopia and hazardous journeys to South Africa.
The 60 interviewees corroborated previous reports of extraordinarily high rates of torture in places of detention in Ethiopia. 26 (43%) had been tortured – 58% of the men and 26% of the women. Of the 38 who had been detained, 68% reported being tortured. All had been severely beaten. 76% of detained men and 54% of detained women were tortured.
Reported conditions of detention in Ethiopia were atrocious. Torture was routinely practised in military camps, prisons, police stations and unofficial places of detention. Methods included arm-tying (falantis), severe enough to cause nerve damage; flaying of the soles of the feet (bastinado); mock execution; whipping; immersion of the head in water and other forms of asphyxiation; walking and running on gravel, barefoot or on knees; suspension by the wrists or ankles; stress positions; sleep deprivation by flooding cells; drenching and other exposure to cold; electrocution; suspension of weights from genitalia; and castration.
Previous reports of high mortality rates among detainees in military camps, especially Hamaresa in E. Hararge, were corroborated by former detainees. In addition to the many who were killed or died in detention, the interviewees reported 91 killings of family and friends.These included 21 summary executions, some of which were public. Interviewees also reported 18 disappearances, ten of close relatives.
Only two of 13 women former detainees were raped in custody, considerably less than the 50% in previous reports, but this probably reflects the small size of the sampled population. Another interviewee was raped in her home by a government official and then in Kakuma camp, Kenya, by an Ethiopian security agent. Three interviewees reported rape of others in Ethiopia, including the multiple gang-rape of a 14 year-old in the Ogaden, who was strangled to death after ten days by the soldiers who raped her.
Although almost all of the abuses were justified by state actors on the basis of victims’ involvement with the Oromo Liberation Front, only half of the interviewees had ever had any personal or family association with the organisation. Only three were themselves involved after the OLF left government in1992.

Monday, August 5, 2013

Sunday, August 4, 2013

OLF: Indiscriminate Killing of Innocent Peoples is a Crime Against Humanity!

The Oromo Liberation Front has learned the cold blooded massacre of our people by TPLF/EPRDF Federal police on August 3, 2013 in Wabe gafarsa village, Kofale town, West Arsi Zone, Oromia state.
The TPLF/EPRDF federal police massacred at least 25 innocent people and wounded hundreds who were peacefully demonstrating against illegal detention of their Imams / mosque leaders/ without arrest warrant. The wounded were taken to local hospitals. After killing and wounding many people, the TPLF/EPRDF federal police has engaged in indiscriminate arrest of thousands innocent people from surrounding communities/ towns/. We strongly condemn this terrorist act of the TLF/EPRDF regime against our people.
Since it came to power, the TPLF/EPRDF regime targeted for massacre the Oromo people in general and the Arsi Oromo in particular that it perceived a threat to its dictatorial minority regime.

Friday, August 2, 2013

የኦሮሞ ተወላጆች ዋሽንግተን ላይ ተሰለፉ

የኦሮሞ ተወላጆች ዋሽንግተን ላይ ተሰለፉ

ከዩናይትድ ስቴትስ የተለያዩ አካባቢዎች የተውጣጡ የኦሮሞ ተወላጆች ዛሬ በዋይት ሃውስ ቤተመንግሥትና በዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ሰልፎችን አካሄደዋል፡፡

በኢትዮጵያ መንግሥት ላይ ያላቸውን ተቃውሞ ያሰሙት ሰልፈኞች ከመልዕክቶቻቸው መካከል

“በምሥራቅ ሐረርጌ እየደረሰ ያለው ግፍ ይቁም፤

በኦሮሞ ምሁራንና ተማሪዎች ላየ እየበረታ ያለው የመብት ረገጣ ይቁም፤ በኦሮሞ ገበሬዎች ላይ እየደረሰ ያለው ከመሬት የማፈናቀል ሥራ ይቁም” የሚሉ ይገኙባቸዋል፡፡
ሰልፉ የተዘጋጀው በኦሮሞ ጥናቶች ማኅበር መሆኑ ታውቋል፡፡

Wednesday, July 24, 2013

ወያኔ በኦነግ አባልነት የሀሰት ክስ አቀናጅቶ በግፍ ባሰረቸው የኦሮሞ ተወላጆች ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ አስተላልፏል።

ወያኔ በኦነግ አባልነት የሀሰት ክስ አቀናጅቶ በግፍ ባሰረቸው የኦሮሞ ተወላጆች ላይ በሚቆጣጠራቸው ዳኞችና አቃቢህጎች አማካኝነት ሽብርተኛ ናቸው በማለት የጥፋተኛነት ፍርድ አስተላልፏል።

በሽብርተኛነት ተፈርጀው ጥፋተኛ ከተባሉት ውስጥ አያሌ የአዳማ፣ የአዲስ አበባ፣ የአዳማ እና የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ይገኙበታል።

*“በኢትዮጵያ ለዓመታት የዘለቀ የሰብአዊ መብት ረገጣ መኖሩ ይታወቃል ይሁንና ለጋሽ ሀገሮች ይህንን ጉዳይ ከግምት ያስገቡ አይመስልም።” አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች!

የኢትዮጵያ መንግስት የሰብዓዊ መብት አያያዝና የለጋሽ አገሮችና ሚና

በኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ትኩረት ሳያደርጉ ዘለቄታ ያለው ልማት ማምጣት የማይቻል መሆኑን በያዝነው ወር ይፋ የሆኑ ሁለት የጥናት ዘገባዎች አመለከቱ። ለጋሽ አገሮች የሚሰጡት ገንዘብ የመብት ጥሰትን ለማባባስ ያለመዋሉን የማረጋገጥ ኃላፊነት እንዳለባቸው ሪፖርቱ ይጠይቃል!!

ጃዋር መሀመድ ኢሳት ከ አድማጭ ለተነሱ ጥያቄዎች ሲመልስ!

   ጃዋር መሀመድ  ኢሳት ከ አድማጭ ለተነሱ ጥያቄዎች ሲመልስ!                             


             

Friday, July 19, 2013

ቂሊንጦ የሚገኙ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አባል የሆኑ እሥረኞች የረሃብ አድማ ላይ ናቸው፡፡



በኢትዮጵያ እሥር ቤቶች ውስጥ በአብዛኛው ታስረው የሚገኙት የኦሮሞ ልጆች ናቸው

በኢትዮጵያ እሥር ቤቶች ውስጥ በአብዛኛው ታስረው የሚገኙት የኦሮሞ ልጆች ናቸው” ያሉት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ዋና ፀሐፊ አቶ በቀለ ነጋ በቅርብ ቀን ደግሞ ከቃሊቲ እሥር ቤት ወደ አንድ መቶ የሚሆኑ እሥረኞች ቂሊንጦ ወደሚባል አቃቂ አካባቢ የሚገኝ እሥር ቤት መወሰዳቸውን አመልክተዋል፡፡

እነዚህ እሥረኞች ከሁለት ዓመታት በላይ ያለፍርድ ታስረው እየተንገላቱና ፍትሕ አጥተው እንደሚገኙ፣ ቤተሰቦቻቸው ለችግር መጋለጣቸውንና መበተናቸውን፣ እነርሱም በእሥር ቤቶቹ ውስጥ ተደጋጋሚ ድብደባ እንደሚፈፀምባቸው አቶ በቀለ ነጋ ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡

አቶ በቀለ አክለውም ሰሞኑኑ እሥረኞቹን ለመጎብኘት ወደዚያው ተጉዘው የነበሩት የአውሮፓ ፓርላማ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚቴ ልዑካን ቡድን አባላት የመንግሥት ፍቃድና ትዕዛዝ ቢይዙም በእሥር ቤቱ ኃላፊዎች እምቢተኝነት ምክንያት ሳያይዋቸው ለመመለስ መገደዳቸውን አመልክተዋል፡፡

እሥረኞቹ እየደረሰብን ነው የሚሉትን እንግልትና ያሉበትን ከባድ ሕይወት እንዲሁም ፍትሕ የዘገየባቸው መሆኑን የሚገልፅ አቤቱታቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ለፍትሕ ሚኒስትሩ፣ ለፓርላማ፣ ለሰብዓዋ መብቶች ኮሚሽን፣ ለእምባ ጠባቂ ኮሚሽን እና ለመሣሰሉት ከፍተኛ የመንግሥት አካላት ማስገባታቸውን አቶ በቀለ ጠቁመዋል፡፡

እየደረሱ ናቸው የሚሏቸው በደሎች ከቁጥጥር ዋጭ የሆኑ እንደሚመስላቸው የተናገሩት አቶ በቀለ ነጋ እሥረኞቹ አሁን የሚገኙት በረሃብ አድማ ላይ መሆኑን አመልክተዋል፡

Tuesday, July 16, 2013

በቂልንጦ እስርቤት የእሰረኞች ደም በድብደባ እንደጎርፍ መፍሰሱን የአይን እማኞች ተናገሩ

በቂልንጦ እስርቤት የእሰረኞች ደም በድብደባ እንደጎርፍ መፍሰሱን የአይን እማኞች ተናገሩ





አርብ ፣ ሀምሌ 6 2005 ዓም በእነ አቶ ተሻለ ኮርኔ መዝገብ የተከሰሱ 69 የኦሮሞ ተወላጆች ፍርድ ቤት መቅረብ ሲገባቸው፣ ፍርድ ቤት የሚወስዳቸው ፖሊስ ያጣሉ። በቅጽል ስሙ ሻእቢያ እየተባለ የሚጠራውን የእስር ቤቱን ሀላፊ ሲጠይቁት ቀጠሮአቸው ለ4 ወር መራዘሙን ይነግራቸዋል። እስረኞቹም ” ከ2 አመታት በላይ የላፍትህ ታስረን በመጨረሻ ብይን በሚሰጥበት ወቅት ለ4 ወራት ተራዝሟል መባሉ ተገቢ አይደለም” በማለት ለጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ የሚላክ ፊርማ ማሰባሰብ ሲጀምሩ ማረሚያ ቤቱ መረጃው ይደርሰውና 69ኙ እሰረኞች በ20 ተከፋፍለው ወደ ተለያዩ የማረሚያ ክፍሎች ወይም ዞኖች እንዲበተኑ ይደረጋል።
አርብ ጧት ሌሎች እስረኞች ወደ ውጭ እንዳይወጡ ከተደረገ በሁዋላ ፣ ሻእቢያ በሚባለው የእስር ቤቱ ሀላፊና ከውጭ በመጡ የፌደራል ፖሊስ አባላት እንዲደበደቡ ይደረጋል። አስተባባሪ ናቸው የተባሉትን 18 እስረኞችን እንደገና በማውጣት በሰደፍና እና በዱላ ከቀጠቀጡዋቸው በሁዋላ 8ቱ ራሳቸውን ሲስቱ ወደ እስር ቤቱ የህክምና ክፍል ይወሰዳሉ። ችግሩ ከአቅሙ በላይ መሆኑን የእስር ቤቱ የህክም ክፍል በመግለጹ፣ በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል።
የአይን እማኞች ለኢሳት እንደገለጹት እስረኞቹ የተደበደቡበት ቦታ በደም በመጨቅየቱ አርብ እለት በውሀ ሲታጠብ አርፍዷል።
ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው መካከል በላይ ኮርሜ ፣ ተፈሪ ቀብኔሳ እና መንግስቱ ግርማ የሚባሉ ይገኙበታል።
በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የአህኮ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና እሰረኞቹ መደብደባቸውንና የተወሰኑት ሆስፒታል መግባታቸውን መረጃው እንደደረሳቸው ገልጸዋል።
ዶ/ር መረራ “ድርጊቱን በተደጋጋሚ ለመንግስት አመልክተን መልስ በማጣታችን መንግስት ሆን ብሎ በፖሊሲ ደረጃ ይዞ የሚያካሄድ ይመስላል” ሲል አክለዋል።
የእስር ቤቱን ሀላፊዎች ለማግኘት ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም።

ኢሳት ዜና

Monday, July 15, 2013

ከ28 በላይ የሚሆኑ የአንድነት አባላት አዲስ አበባ ውስጥ በፖሊስ ታገቱ

ሰበር ዜና

በጎንደርና በደሴ በደረሰበት ፖለቲካዊ ኪሳራ የተበሳጨው ኢህአዴግ ዛሬ ከ28 በላይ የሚሆኑ የአንድነት ፓርቲ አባላትን በተለያዩ የአዲስ አበባ አካባቢዎች አግቷል፡፡ የታጋቾቹን ስም ዝርዝርና የታሰሩባቸውን አከባቢዎች ከደቂቃዎች በኋላ ይፋ እናደርጋለን፡፡

Sunday, July 14, 2013

የኢትዮጵያ ህዝብ ለነፃነቶ ተነስታል ብረት ሊያስቆመው የማይችለው ትግል ተቀጣጥላል!!!


የኢትዮጵያ ህዝብ ለነፃነቶ ተነስታል ብረት ሊያስቆመው የማይችለው ትግል ተቀጣጥላል!!!

                              1 . ፍርሃት የወለደው ታጋሽነት .....ለብዙ ሕግወጥ ድርጊት ዳርጎናል !!!
                                        
2. የታሰሩት የህሊናና የፓለቲካ እሰረኞች ባሰቸኳይ ይፈቱ !!

3 . ውሽት ሰልችቶናል ይቁም !!

4 . በፈጠራ ክስ በዜጎች ላይ የሚፈፀመው ግፍ ባሰቸኳይ ይቁም !

                                                 
አንድነት ፓርቲ በጎንደርና በደሴ የሚያካሂደውን ሰላማዊ ሰልፍ 






የኢትዮጵያ ህዝብ ለነፃነቶ ተነስታል ብረት ሊያስቆመው የማይችለው ትግል ተቀጣጥላል!!!





Saturday, July 13, 2013

Tuesday, July 9, 2013

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ የችሎት ውሎ

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ቀደም ሲል ግንቦት 22/2005 ዓ.ም በዋለው ችሎት በሰጠው ትዕዛዝ መሠረት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ የመከላከያ ምሥክሮቹን ዛሬ - ማክሰኞ ሐምሌ 2/2005 ዓ.ም ማሰማት ጀምሯል፡፡

ዶ/ር ያሬድ ለገሠ እና ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ለምሥክርነት ቀርበዋል፡፡

“የመንግሥትን ስም ማጥፋት” የሚለው ድንጋጌ ሃሣብን ከመግለፅ መብትና ከሃገሪቱ ሕገመንግሥትም ጋር የሚቃረን መሆኑን የሕግ ምሁሩ ዶ/ር ያሬድ ለገሠ ለፍርድ ቤት ገልፀዋል፡፡

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ ‘የመንግሥት ድርጊቶች ናቸው’ ብሎ የዘረዘራቸው በሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ - ሰመጉ ሪፖርቶች የተረጋገጡ መሆናቸውንም የድርጅቱ መሥራችና የቀድሞ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡

ሦስተኛውን የመከላከያ ምሥክር ለመስማት በዕለቱ ጊዜ የሌለው መሆኑን ፍርድ ቤቱ ካስረዳ በኋላ ለሐምሌ 23/2005 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡