Wednesday, July 24, 2013

ወያኔ በኦነግ አባልነት የሀሰት ክስ አቀናጅቶ በግፍ ባሰረቸው የኦሮሞ ተወላጆች ላይ የጥፋተኛነት ፍርድ አስተላልፏል።

ወያኔ በኦነግ አባልነት የሀሰት ክስ አቀናጅቶ በግፍ ባሰረቸው የኦሮሞ ተወላጆች ላይ በሚቆጣጠራቸው ዳኞችና አቃቢህጎች አማካኝነት ሽብርተኛ ናቸው በማለት የጥፋተኛነት ፍርድ አስተላልፏል።

በሽብርተኛነት ተፈርጀው ጥፋተኛ ከተባሉት ውስጥ አያሌ የአዳማ፣ የአዲስ አበባ፣ የአዳማ እና የሀረማያ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ይገኙበታል።

*“በኢትዮጵያ ለዓመታት የዘለቀ የሰብአዊ መብት ረገጣ መኖሩ ይታወቃል ይሁንና ለጋሽ ሀገሮች ይህንን ጉዳይ ከግምት ያስገቡ አይመስልም።” አለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች!

የኢትዮጵያ መንግስት የሰብዓዊ መብት አያያዝና የለጋሽ አገሮችና ሚና

በኢትዮጵያ በሰብዓዊ መብት አያያዝ ላይ ትኩረት ሳያደርጉ ዘለቄታ ያለው ልማት ማምጣት የማይቻል መሆኑን በያዝነው ወር ይፋ የሆኑ ሁለት የጥናት ዘገባዎች አመለከቱ። ለጋሽ አገሮች የሚሰጡት ገንዘብ የመብት ጥሰትን ለማባባስ ያለመዋሉን የማረጋገጥ ኃላፊነት እንዳለባቸው ሪፖርቱ ይጠይቃል!!

ጃዋር መሀመድ ኢሳት ከ አድማጭ ለተነሱ ጥያቄዎች ሲመልስ!

   ጃዋር መሀመድ  ኢሳት ከ አድማጭ ለተነሱ ጥያቄዎች ሲመልስ!                             


             

Friday, July 19, 2013

ቂሊንጦ የሚገኙ የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ አባል የሆኑ እሥረኞች የረሃብ አድማ ላይ ናቸው፡፡



በኢትዮጵያ እሥር ቤቶች ውስጥ በአብዛኛው ታስረው የሚገኙት የኦሮሞ ልጆች ናቸው

በኢትዮጵያ እሥር ቤቶች ውስጥ በአብዛኛው ታስረው የሚገኙት የኦሮሞ ልጆች ናቸው” ያሉት የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስ ዋና ፀሐፊ አቶ በቀለ ነጋ በቅርብ ቀን ደግሞ ከቃሊቲ እሥር ቤት ወደ አንድ መቶ የሚሆኑ እሥረኞች ቂሊንጦ ወደሚባል አቃቂ አካባቢ የሚገኝ እሥር ቤት መወሰዳቸውን አመልክተዋል፡፡

እነዚህ እሥረኞች ከሁለት ዓመታት በላይ ያለፍርድ ታስረው እየተንገላቱና ፍትሕ አጥተው እንደሚገኙ፣ ቤተሰቦቻቸው ለችግር መጋለጣቸውንና መበተናቸውን፣ እነርሱም በእሥር ቤቶቹ ውስጥ ተደጋጋሚ ድብደባ እንደሚፈፀምባቸው አቶ በቀለ ነጋ ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡

አቶ በቀለ አክለውም ሰሞኑኑ እሥረኞቹን ለመጎብኘት ወደዚያው ተጉዘው የነበሩት የአውሮፓ ፓርላማ የሰብዓዊ መብቶች ኮሚቴ ልዑካን ቡድን አባላት የመንግሥት ፍቃድና ትዕዛዝ ቢይዙም በእሥር ቤቱ ኃላፊዎች እምቢተኝነት ምክንያት ሳያይዋቸው ለመመለስ መገደዳቸውን አመልክተዋል፡፡

እሥረኞቹ እየደረሰብን ነው የሚሉትን እንግልትና ያሉበትን ከባድ ሕይወት እንዲሁም ፍትሕ የዘገየባቸው መሆኑን የሚገልፅ አቤቱታቸውን ለጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ለፍትሕ ሚኒስትሩ፣ ለፓርላማ፣ ለሰብዓዋ መብቶች ኮሚሽን፣ ለእምባ ጠባቂ ኮሚሽን እና ለመሣሰሉት ከፍተኛ የመንግሥት አካላት ማስገባታቸውን አቶ በቀለ ጠቁመዋል፡፡

እየደረሱ ናቸው የሚሏቸው በደሎች ከቁጥጥር ዋጭ የሆኑ እንደሚመስላቸው የተናገሩት አቶ በቀለ ነጋ እሥረኞቹ አሁን የሚገኙት በረሃብ አድማ ላይ መሆኑን አመልክተዋል፡

Tuesday, July 16, 2013

በቂልንጦ እስርቤት የእሰረኞች ደም በድብደባ እንደጎርፍ መፍሰሱን የአይን እማኞች ተናገሩ

በቂልንጦ እስርቤት የእሰረኞች ደም በድብደባ እንደጎርፍ መፍሰሱን የአይን እማኞች ተናገሩ





አርብ ፣ ሀምሌ 6 2005 ዓም በእነ አቶ ተሻለ ኮርኔ መዝገብ የተከሰሱ 69 የኦሮሞ ተወላጆች ፍርድ ቤት መቅረብ ሲገባቸው፣ ፍርድ ቤት የሚወስዳቸው ፖሊስ ያጣሉ። በቅጽል ስሙ ሻእቢያ እየተባለ የሚጠራውን የእስር ቤቱን ሀላፊ ሲጠይቁት ቀጠሮአቸው ለ4 ወር መራዘሙን ይነግራቸዋል። እስረኞቹም ” ከ2 አመታት በላይ የላፍትህ ታስረን በመጨረሻ ብይን በሚሰጥበት ወቅት ለ4 ወራት ተራዝሟል መባሉ ተገቢ አይደለም” በማለት ለጠቅላይ ሚኒስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ የሚላክ ፊርማ ማሰባሰብ ሲጀምሩ ማረሚያ ቤቱ መረጃው ይደርሰውና 69ኙ እሰረኞች በ20 ተከፋፍለው ወደ ተለያዩ የማረሚያ ክፍሎች ወይም ዞኖች እንዲበተኑ ይደረጋል።
አርብ ጧት ሌሎች እስረኞች ወደ ውጭ እንዳይወጡ ከተደረገ በሁዋላ ፣ ሻእቢያ በሚባለው የእስር ቤቱ ሀላፊና ከውጭ በመጡ የፌደራል ፖሊስ አባላት እንዲደበደቡ ይደረጋል። አስተባባሪ ናቸው የተባሉትን 18 እስረኞችን እንደገና በማውጣት በሰደፍና እና በዱላ ከቀጠቀጡዋቸው በሁዋላ 8ቱ ራሳቸውን ሲስቱ ወደ እስር ቤቱ የህክምና ክፍል ይወሰዳሉ። ችግሩ ከአቅሙ በላይ መሆኑን የእስር ቤቱ የህክም ክፍል በመግለጹ፣ በአምቡላንስ ወደ ሆስፒታል ተወስደዋል።
የአይን እማኞች ለኢሳት እንደገለጹት እስረኞቹ የተደበደቡበት ቦታ በደም በመጨቅየቱ አርብ እለት በውሀ ሲታጠብ አርፍዷል።
ከፍተኛ ጉዳት ከደረሰባቸው መካከል በላይ ኮርሜ ፣ ተፈሪ ቀብኔሳ እና መንግስቱ ግርማ የሚባሉ ይገኙበታል።
በጉዳዩ ዙሪያ ያነጋገርናቸው የአህኮ ሊቀመንበር ዶ/ር መረራ ጉዲና እሰረኞቹ መደብደባቸውንና የተወሰኑት ሆስፒታል መግባታቸውን መረጃው እንደደረሳቸው ገልጸዋል።
ዶ/ር መረራ “ድርጊቱን በተደጋጋሚ ለመንግስት አመልክተን መልስ በማጣታችን መንግስት ሆን ብሎ በፖሊሲ ደረጃ ይዞ የሚያካሄድ ይመስላል” ሲል አክለዋል።
የእስር ቤቱን ሀላፊዎች ለማግኘት ሙከራ ብናደርግም አልተሳካልንም።

ኢሳት ዜና

Monday, July 15, 2013

ከ28 በላይ የሚሆኑ የአንድነት አባላት አዲስ አበባ ውስጥ በፖሊስ ታገቱ

ሰበር ዜና

በጎንደርና በደሴ በደረሰበት ፖለቲካዊ ኪሳራ የተበሳጨው ኢህአዴግ ዛሬ ከ28 በላይ የሚሆኑ የአንድነት ፓርቲ አባላትን በተለያዩ የአዲስ አበባ አካባቢዎች አግቷል፡፡ የታጋቾቹን ስም ዝርዝርና የታሰሩባቸውን አከባቢዎች ከደቂቃዎች በኋላ ይፋ እናደርጋለን፡፡

Sunday, July 14, 2013

የኢትዮጵያ ህዝብ ለነፃነቶ ተነስታል ብረት ሊያስቆመው የማይችለው ትግል ተቀጣጥላል!!!


የኢትዮጵያ ህዝብ ለነፃነቶ ተነስታል ብረት ሊያስቆመው የማይችለው ትግል ተቀጣጥላል!!!

                              1 . ፍርሃት የወለደው ታጋሽነት .....ለብዙ ሕግወጥ ድርጊት ዳርጎናል !!!
                                        
2. የታሰሩት የህሊናና የፓለቲካ እሰረኞች ባሰቸኳይ ይፈቱ !!

3 . ውሽት ሰልችቶናል ይቁም !!

4 . በፈጠራ ክስ በዜጎች ላይ የሚፈፀመው ግፍ ባሰቸኳይ ይቁም !

                                                 
አንድነት ፓርቲ በጎንደርና በደሴ የሚያካሂደውን ሰላማዊ ሰልፍ 






የኢትዮጵያ ህዝብ ለነፃነቶ ተነስታል ብረት ሊያስቆመው የማይችለው ትግል ተቀጣጥላል!!!





Saturday, July 13, 2013

Tuesday, July 9, 2013

የጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ የችሎት ውሎ

የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16ኛ ወንጀል ችሎት ቀደም ሲል ግንቦት 22/2005 ዓ.ም በዋለው ችሎት በሰጠው ትዕዛዝ መሠረት ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ የመከላከያ ምሥክሮቹን ዛሬ - ማክሰኞ ሐምሌ 2/2005 ዓ.ም ማሰማት ጀምሯል፡፡

ዶ/ር ያሬድ ለገሠ እና ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ለምሥክርነት ቀርበዋል፡፡

“የመንግሥትን ስም ማጥፋት” የሚለው ድንጋጌ ሃሣብን ከመግለፅ መብትና ከሃገሪቱ ሕገመንግሥትም ጋር የሚቃረን መሆኑን የሕግ ምሁሩ ዶ/ር ያሬድ ለገሠ ለፍርድ ቤት ገልፀዋል፡፡

ጋዜጠኛ ተመስገን ደሣለኝ ‘የመንግሥት ድርጊቶች ናቸው’ ብሎ የዘረዘራቸው በሰብዓዊ መብቶች ጉባዔ - ሰመጉ ሪፖርቶች የተረጋገጡ መሆናቸውንም የድርጅቱ መሥራችና የቀድሞ ሊቀመንበር ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም ለፍርድ ቤቱ አስረድተዋል፡፡

ሦስተኛውን የመከላከያ ምሥክር ለመስማት በዕለቱ ጊዜ የሌለው መሆኑን ፍርድ ቤቱ ካስረዳ በኋላ ለሐምሌ 23/2005 ዓ.ም ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

Saturday, July 6, 2013

The untold story of Oromo freedom fighter, Jaarraa Abbaa Gadaa









The untold story of Oromo freedom fighter, Jaarraa Abbaa Gadaa
Photo: File – (Left to Right) – Oromo Freedom Fighters Elemoo Qilixuu, Jaarraa Abbaa Gadaa, and Muhaammad Umar in Aden, Yemen, in 1969.
The Oromo freedom fighters led by Elemoo Qilixuu participated at the foundation of the Oromo Liberation Front in Dec-Jan 1974 in Finfinnee along with leaders of the underground Macha-Tuullama youth movement, and went on to resume the armed resistance against the Abyssinian colonial forces in the highlands of Charchar, Eastern Oromia. However, the armed resistance led by Elemoo Qilixuu was short-lived due to the martyrdom of Elemoo in Sept 1974. While the Oromofreedom fighters led by Jaarraa AbbaaGadaa en route to eastern Oromia were detained by the Somali government, and upon his release in 1975 from the Somali prison, Jaarraa Abbaa Gadaa joined representatives of the underground study cells of the OLF, individual Oromo nationalists andpatriots for the “Founding Congress” of the OLF in June 1976, at which pointthe 1974 draft program was revised and a new detailed political program of the Front was issued. More on the Birth of the OLF can be found on the Oromo Chronology @ Gadaa.com .
( OPride.com ) — Ibro Shaxa was killed at the battle of Ciracha during Egyptian invasion of Harar led by Rauf Pasha in 1876. He left behind a teenage son, Hamid. Unlike his father, Hamid, was poisoned by Menelik after the battle of Calanqo (1887) in which the Abyssinian army defeated Oromo fighters. Hamid, too, left his young son, Ibrahim, behind.
Abdulkarim Ibrahim was born in 1936,at a time when Abyssinian feudal lords usurped Oromo lands and subjected the farmers to a life of servitude. The son of Haji Ibrahim Hamid Ibro Shaxa, Abdulkarim — better know as Jaarraa Abbaa Gadaa — was born in Eastern Oromia, near Gara Mulata, at a village of Mudir Goro,to a generation of men who have diedfighting long and hard.
From an early age, in and outside of school, his peers knew Jaarraa as a respectful and humble friend. Compassionate by nature, the soft hearted Jaarraa was known for helping the needy. As he came of age, Jaarraa began seeing notable differences between the haves and have not’s, the troublemakers and thetroubled among his rural community. He soon realized that the Oromo wereseen as inferiors and relegated to second-class status on their own land. He demurred at those who attemptedto fit-in with others by accepting what was imposed on them instead of revolting against the status quo and fighting for their freedom.
Wherever he went, the young Abdulkarim spoke proudly in Afan Oromo, at a time when the language was not favored. Proud of his culture and heritage, Abdulkarim began teaching others about it. After completing secondary education at the city of Harar, in Eastern Ethiopia, the suffering of Oromo people began to weigh heavily on his soul. Though he had a promising educational and political career as one of the few Oromos who completed secondary school in those days, he was most concerned with Oromo people’s freedom and dignity. At the height of his youth, Jaarraa left school and wentto Asabot, also in Eastern Oromia, to prepare for a journey that would shape the rest of his life — taking himaround the world for nearly half a century.